የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የስደት ተመላሾችን መልሶ ለማቋቋም ከተለያዩ ተቋማት ጋር በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረመ
የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የስደት ተመላሾችን መልሶ ለማቋቋምና ጥቅማቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ሥምምነት አደረገ። የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከፍትሕ ሚኒስቴር፣ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከግብርና ሚኒስቴር እና ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር ሥምምነት አድርጓል። በተጨማሪም ከፌዴራል ፖሊስ፣ ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ እንዲሁም ከስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ጋርም…
