የክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የፎቶግራፍ አውደርእይ አካሄደ ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ በ2016 በክልሉ በመንግሥትና አጋር አካላት የተሰሩ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን የሚያስቃኝ የፎቶግራፍ ኢግዚቢሽን በታርጫ ከተማ አካሂዷል። የፎቶግራፍ ኢግዚቢሽኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢንጂነር)፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ፣የክልሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የክልሉ መንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና…
