Trendings

BLOGS

የልማት ክፍተቶችን ለመፍታት በተሰሩ ሥራዎች ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ :- ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በምዕራብ ኦሞ ዞን የባቹማ ኮንስትራክሽን እና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። በምረቃው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደገለጹ፤ በክልሉ በመንግሥትና ፓርቲው መሪነት ባለፉት ዓመታት የልማት ውስንነት ባለባቸው አከባቢዎች የልማት ክፍተቶችን በመፍታት ረገድ ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በተለያዩ ምክንያቶች ፍትሃዊ የልማት ሥርጭት ባልተካሄደባቸው…

Read More

በክልሉ የቀጠለዉ የተ.መ.ድ ከፍተኛ አመራሮች ጉብኝት

ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሥራ ኃላፊዎች ለሥራ ጉዳይ ወደ ታርጫ ከተማ ገቡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እና ሰሞኑን በክልሉ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሥራ ኃላፊዎችና ተወካዮች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት በዳዉሮ ዞን ታርጫ ከተማ ገብተዋል። ወደ…

Read More

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንደ ክልል ያጋጠመንን የአገልግሎት አሰጣጥ ስብራት እያከመ መሆኑ ተገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በ5 ዞንና በ 15 ከተማ አስተዳደሮች ተጨማሪ አገልግሎት እንደሚጀመርም ተገልጿል። እንደ ሀገር በየዘርፉ የሚታዩ የአገልግሎት አሰጣጥ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ የህዝቡን ምሬት አግዝፈወት ቆይተዋል። መንግስትም ችግሩን ለመቅረፍ እና ለመፍትሄውም ” መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን “ወደ ስራ አስገብቷል ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ብዝሀ ከተሞች ውስጥ አንዷ በሆነች ሚዛን-አማን…

Read More

የኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ዘርፍን ለማጠናከር ያለመ ዉይይት በዳዉሮ ዞን ተካሄደ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት በዳዉሮ ዞን የኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ሥራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ያለመ የውይይት መድረክ በዳውሮ ዞን ተካሂዷል። በክልሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ በአቶ የሺዋስ ዓለሙ የተመራ የአመራር ቡድን ከዞኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በየደረጃው የሚገኙ የኮሙኒኬሽን መዋቅሮችን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ሰፊ ምክክር አድርጓል። የሚዲያ ሚና ለልማት ስኬት ወሳኝ ነው አቶ…

Read More

የምግብ ስርዓት ለውጥ ፍኖተ ካርታና ክላስተር 7 ማስተዋወቂያ ስልጠና በቦንጋ ከተማ ተጀመረ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የምግብ ሰርዓትና የስርዓተ–ምግብ ፕሮግራም ማስተባበሪያ ዩኒት ከአግሪካልቸራል ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት (ATI) ጋር በመተባበር በ“የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን የፍኖተ ካርታ ወርክሾፕ እና ክላስተር 7 ግንዛቤ” በሚል ርዕስ በተዘጋጀ የውይይትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ፕሮግራም በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል። ስልጠናው በክልሉ የምግብ ስርዓትን በዘላቂነት፣ በተቀናጀ አቀራረብ እና በክላስተሪንግ ስርዓት ለመለወጥ የሚያግዙ ዋና ዋና አቅጣጫዎች ላይ…

Read More

በመግባባት ላይ የተመሰረተ የምክክር ሂደት ማካሄድ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ መስጠት ነው ብሔራዊ መግባባትን ለማጠናከር በመግባባት ላይ የተመሰረተ የምክክር ሂደት ማካሄድ ለዘላቂ ሰላም ዋጋ መስጠት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) አመራር አባላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው። በዚሁ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርዓያ ኮሚሽኑ በአጀንዳ ማሰባሰብና ተሳታፊ ልየታ የተከናወኑ ተግባራትን ገለፃ አድርገዋል። ኢትዮጵያ ያለፈችባቸው የግጭት አዙሪት የተሳሳቱ መንገዶች በሀገራዊ ምክክር መፍትሔ ሊያገኙ እንደሚገባ የዘመናት ጥያቄ ሆኖ መቆየቱን ተናግረዋል። ዘላቂ ብሔራዊ መግባባትን…

Read More

የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።

መንገድ ትራፊክ አደጋ መጠን ለመቀነስና የማሽከርከር ስነ-ባህርይ ላይ በክልላችን ሁሉም ዞኖች የነባር አሽከርካሪዎች ተሃድሶ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት የቢሮ ምክትል ኃላፊና የትራንስፖርት ዘርፍ ኃላፊ ኢንጅነር ዘመዴ አንዳርጌ እንዳሉት በክልሉ ለ19 ሺህ ነባር አሽከርካሪዎች የተሃድሶ ስልጠና በ32 ማዕከላት እየተሰጠ እንደሆነ ገልጸዋል። ኃላፊው ስገልፁ በግል በማህበራትና በመንግስት ተቋማት ሥር…

Read More

ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የኢቢሲ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር የሆኑትን ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢነት ሹመትን አፀደቀ። ምክር ቤቱ ለኮርፖሬሽኑ ቦርድ አባልነት የቀረቡ ዘጠኝ ዕጩዎችን ሹመት አፅድቋል። በዚህም፦ ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት – የቦርዱ ሰብሳቢ (የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ…

Read More

የዲዚ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ የምስጋና በአል “ከያ ቢያርግ” መከበሩ ባህላቸውን ወደፊት እንዲወጣ እድል እንደፈጠረላቸው የቤሮ ወረዳ ነዋሪዎች ተናገሩ

በአሉን የማስተዋወቅ ወደፊት የማውጣት ስራ ተጠናክሮ እንደሚሰራ የቤሮ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አራጋው ይመር አስታውቀዋል። የዲዚ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በአል “ከያ ቢያርግ” የተጣላ የሚታረቅበት፣ የደረሰ እህል የሚቀመስበት፣ ለቀጣይ አዝመራ የእርሻ መሳሪያዎች ለእርሻ የሚዘጋጁበት በመሆኑ በአሉ በብሔረሰቡ ዘንድ ታላቅ ትርጉም ያለው መሆኑ ተጠቁሟል። በአሉ በባለፉት ሀምሳ አመታት ተቋርጦ የነበረ ሲሆን ዘንድሮ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው።…

Read More

ተቋማዊ አቅምን በመገንባት የመረጃ ተደራሺነትን ለማረጋገጥ የተሰራዉ ሥራ አበረታች መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት ገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ፣ መረጃን ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግና ተቋማዊ አሠራርን ለማዘመን የጀመራቸው ሥራዎች ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ መሆኑን የክልሉ ምክር ቤት የማኅበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ። ኮሚቴው የቢሮውን የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት የሥራ አፈፃፀም በገመገመበት ወቅት እንደተገለጸው፤ ተቋሙ የመረጃ አቅርቦትን ጥራት ለማረጋገጥና የቴክኖሎጂ አማራጮችን ለማስፋት የሄደበት ርቀት አበረታች ነው። በግምገማ…

Read More