Trendings

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የእሳት አደጋ እየተከሰተ በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ የክልሉ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢንጂነር አስራት ገብረማርያም አሳሰቡ።

በክልሉ ከሽካ ዞን በስተቀር በአምስት ዞኖች ስፋቱና የጉዳቱ መጠን የተለያየ የደን እሳት ቃጠሎ መከሰቱን አስታውቀዋል። በካፋ ዞን በጠሎ እና በአዲዮ ወረዳዎች አዋሳኝ አካባቢ ደን ላይና በዴቻ ወረዳ ዳኪቲ ቀበሌ እንዲሁም በገዋታ ወረዳ የደን ቃጠሎ ተከስቶ ማህበረሰቡን በማስተባበር ለመቆጣጠር እየተሠራ ነው ብለዋል። በዳውሮ ዞን ማረቃ አደአ፣ ማሪ ወረዳ፣ ታርጫ ዙሪያ ወረዳ እና ሎማ ወረዳ የእሳት ቃጠሎ…

Read More

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቤንች ሸኮ ዞን ተወካዮች ከዞኑ የካቢኔ አባላት ጋር በዞናዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እያካሄዱ ነው።

የፓርላማ አባላቱ በቀጣይም በዞኑ በትምህርት ፣ ጤና ፣ የመንገድ እና የውሀ ልማት ስራዎችን ተዘዋውረው የሚጎበኙ ሲሆን ከወከሏቸው ህዝብ ጋር ውይይት እንደሚያደርጉም ገልጸዋል። የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን እንደተናገሩት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዞኑ ተወካዮች በተለያዩ ጊዜያት ወደ ህዝቡ እየወረዱ የተለያዩ የልማት ስራዎችን የመጎብኘትና ከወከሉት ህዝብ ጋር መድረኮችን እየፈጠሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል። የምክር ቤት…

Read More

የህዝብ ውይይት መድረኮችን በማጠናከር በከተሞች የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በከተሞች የመልካም አስተዳደርና የልማት ተግባራት ላይ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ በቦንጋ እያካሄደ ነው። በምክክር መድረኩ የተገኙት የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር የማታለም ቸኮል የመድረኩ ዓላማ ሀገራችን ለከተማ ልማት ከሰጠችው ትኩረት፣ ከከተሞች ተለዋዋጭ ባህሪና የህዝብ ቁጥር በየጊዜው ከመጨመር አንጻር ስራው ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ እስካሁን የመጡ ለውጦችን…

Read More

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፎረም በደቡብ ኮሪያ ተካሄደ

ከ200 በላይ የሚሆኑ የኩባንያ ባለቤቶች በተገኙበት የኢትዮጵያን እምቅ የኢንቨስትመንት እድል ለኢንቨስተሮች የሚያስተዋውቅ ፎረም በደቡብ ኮሪያ ሴዑል ተካሂዷል፡፡ በዝግጅቱ ላይ በደቡብ ኮሪያ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ደሴ ዳልኬ÷ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የተሻለ የኢንቨስትመንት አማራጮች እና ማበረታቻዎች እንዳላት አስገንዝበዋል፡፡ በኢትዮጵያ ምቹ የኢንቨስትመንት ምህዳር ለመፍጠር በመንግስት የተደረጉ ፖሊሲ ማሻሻያችን፣ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ማበረታቻዎች እና ምቹ የንግድ…

Read More

ከተሞች ለነዋሪዎች የተመቹ እንዲሆኑ የተጀመሩ ጥረቶች ለውጥ እያመጡ መሆናቸውን የደካ እና ጀሙ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች ገለጹ

ደካ እና ጀሙ ከተማ አስተዳደሮች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት በካፋ እና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች ከሚገኙ ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች መካከል ተጠቃሾች ናቸው። ሁለቱ ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች በ2013 ዓ.ም በፈርጅ ሶስት የታቀፉ ከተሞች ሲሆኑ እነዚህን ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ ሰፊ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። የደካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ በላይ ባደገ እንደገለጹት፤ ደካ ከተማን ለነዋሪዎች ለመኖሪያ…

Read More

ሁሉንም የገቢ አርዕስቶች ለይቶ በአግባቡ በመሰብሰብ የህብረተሰቡን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ መረባረብ ያስፈልጋል፦አቶ አበበ ማሞ

የሸካ ዞን ገቢዎች መምሪያ የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀምና በቀሪ ወራት ትኩረት አቅጣጫ ዙሪያ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የምክክር መድረክ በማሻ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ በመድረኩ ላይ ተገኝተው ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ገቢ ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ስራዎችን ለማሳካት ትልቅ ድርሻ አለው ብለዋል። በዞኑ በ2017 በጀት ዓመት ከ1.1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ…

Read More

የሚዲያ ተቋማት ፈጣን ፣ ጥራትና ዘመናዊ የሚዲያ አስተዳደርን በማስፋት ለአድማጭ ተመልካቹ ተደራሽ ሊሆኑ ይገባል ፦ አቶ የሺዋስ ዓለሙ

የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ የ2017 የመጀመሪያ ግማሽ አመት ዕቅድ አፈጻጸም መድረክ በሚዛን አማን ተካሂዷል። የቅርንጫፍ ጣቢያው የልማት ዕቅድና በጀት አስተዳደር ባለሙያ አቶ መካሻው ከበደ ባቀረቡት የ6 ወራት ሪፖርት ጣቢያው በቤንች ሸኮና ምዕራብ ኦሞ ዞን በሚገኙ 5 ቋንቋዎች የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በግማሽ ዓመቱ በሬዲዮ ኬዝ 5ሺ 210 የሬዲዮ ዜናዎች ፣…

Read More

“ሪፖርታዥ”

ፋና ወጊው “የእሞታ” አዳሪ ትምህርት ቤት ኮንታ ዞን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ከሚገኙ ስድስት ዞኖች አንዱ ነው ። ዞኑ የተለያዩ የተፈጥሮ ሀብት ለም መሬት፣ ቱባ ባህልና የቱርስት መዳረሻዎች ያሉበት ለዓይን የሚማረክ የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ እና በገበታ ለሀገር የተሰራ የዝሆን ዳና ሎጅን ባለቤት መሆኑን ለአብነት መጥቀስ ይቻላል ። በዞኑ ውስጥ በማህበራዊ ልማት ዘርፍ…

Read More

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ 397 ተማሪዎችን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ።

ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ባከናወነው የምረቃ ስነ-ስርዓት 397 ተማሪዎችን አስመርቋል። የዘንድሮው ምረቃ ለ5ኛ ጊዜ የተከናወነ ሲሆን በመርሃ-ግብሩ ከመደበኛ ተማሪዎች በተጨማሪ የማታ ፣ የሳምንቱ መጨረሻ እንዲሁም የክረምት ተማሪዎችም ተካተዋል። የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዼጥሮስ ወ/ጊዮርጊስ ባስተላለፉት መልእክት የዛሬውን ሳይጨምር ባለፉት አራት ምረቃዎች ከ4000 በላይ ተማሪዎችን አስመርቀናል ያሉ ሰሆን በተለይ የዛሬው የጤና ሳይንስና የካፊኖኖ ትምህርት ክፍል ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ…

Read More

የፓርቲው ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ሁሉ አቀፍ ተፈጻሚነታቸው እንዲረጋገጥ የህዝቡ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ

ከሚዛን አማን ከተማ ነዋሪዎች ጋር የተካሄደው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ በሁለተኛው የፓርቲው ጉባኤ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ላይ በሰፊው መክሯል። የመድረኩ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በስልጣን ዘመናቸው ሁለት ጊዜ ወደ ዞናችን በመምጣትና ሁለት ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ወደ ስራ በማስገባታቸው እናመሰግናለን ብለዋል። የቤንች ሸኮ ዞን የወርቅ ክምችት ያለበት ፣ ለኤክስፖርት የሚሆኑ ቡና ፣ ቅመማ ቅመምና ሰብሎች የሚመረቱባት…

Read More