በግብርናው ዘርፍ የተያዙ ኢኒሼቲቮችን ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኮንታ ዞን ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ መምሪያ አስታወቀ ።
መምሪያው በግብርና ዘርፍ የልማት ስራዎች የሚያበረታቱ ተግባራት መኖራቸውንም ገልጿል ። በኮንታ ዞን በግብርና ልማት ስራዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጡ ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በዞኑ በተከናወኑ የልማት ስራዎችም የአካባቢው አርሶ አደሮች ከማምረት ባለፈም ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ በኢኮኖሚው ተጠቃሚ መሆን ስለመቻላቸው ተናግረዋል ። በአመያ ዙሪያ ወረዳ የ01 ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ትዕግስት ከበደ በከተማው በተፈጠረ የሴቶች…
