በክልሉ በመሠረተ ልማት እና በማህበራዊ ዘርፎች የህዝብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራትን ማከናወን ተችሏል።ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር)
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በብልጽግና ፓርቲ የመጀመሪያው ጉባኤው አቅጣጫ መነሻ በክልሉ በመሠረተ ልማትና ማህበራዊ ዘርፎች በተሰሩ ሥራዎችና በተገኙ ውጤቶች ላይ ከሚዲያዎች ጋር ቆይታ አድርጓል። ርዕሰ መስተዳድሩ በቆይታቸውም፤ባለፉት ሶስት ዓመታት በመሠረተ-ልማት እና በማህበራዊ ዘርፎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ሥራዎች መከናወናቸውና በዚህም እምርታዊ ውጤቶች መመዘገባቸውን ገልጸዋል። በክልሉ ሰፊና ትልቁ ተግዳሮት…
