ከ2015 የግብር ዘመን ከደረጃ “ለ”ና “ሐ” ግብር ከፋዮች ከ294 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል ።የክልሉ ገቢዎች ቢሮ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2015 የግብር ዘመን ከደረጃ “ለ” ግብር ከፋዮች በወቅቱና በቅጣት እንዲሁም ከንግድ ዘርፍና ከቤት አከራይ ከደረጃ “ሐ” ግብር ከፋዮች እስከ መስከረም 29/2016 ዓ.ም 294 ሚሊዮን 656 ሺህ 341 ብር ከ 49 ሳንቲም መሰብሰብ መቻሉን ገልፆ ይህም ለመሰብሰብ ከታቀደው 71.1 ከመቶ መሆኑን ገልጿል። ከተሰበሰበው ገቢ 244 ሚሊዮን 921 ሺህ 605…

Read More

ሰንደቅ ዓላማ የሀገር ሉዓላዊነት መገለጫና መከበሪያና የአንድነታችን መሠረት ነው :-ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል 16ኛው የሰንደቅ ዓለማ ቀን ” የሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ ለህብረብሔራዊ አንድነታችንና ለሉዓላዊነታችን ዋስትና “! በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ሁነቶች በቦንጋ ማዕከል ተከብሯል ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በወቅቱ እንደገለፁትኢትዮጵያ ብዙ ቀለማት፣ብሔር ብሔርሰቦችና ህዝቦች የሚገኙባት ሀገር ናት ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በብሔር፣ በጎሳና በቋንቋ…

Read More

16ኛው ብሄራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በተለያዩ ሁነቶች እንደሚከበር ተገለፀ ።

” የሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ ለህብረ ብሄራዊ አንድነታችንና ሉአላዊነታችን ዋስትና ነው” ! በሚል መሪ ቃል በክልላችን ጥቅምት 5/2016 የተለያዪ ወቅታዊ መልዕክቶችን በማስተላለፍ እንደሚከበር የክልሉ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ ተናግረዋል። ዋና አፈጉባኤው በዕለቱ የሚከበረው 16ኛውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን የተለያዩ መልዕክቶችን በማስተላለፍ እንደሚከበርና ለዚህም አስፈላጊው ዝግጅቶች መከናወናቸውን ተናግረዋል ። በዕለቱም ሰንደቅ ዓላማችንን በተመለከቱ በተለያዩ ዝግጅቶች…

Read More

በመሬት አያያዝና አስተዳደር የአየር ንብረት ማሻሻያ (CALM) ፕሮግራም በክልሉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ውጤታማ እንደሆነ ተገለጸ።

በክልሉ ግብርና ቢሮ ስር በመሬት አያያዝና አስተዳደር የአየር ንብረት ማሻሻያ መርሀግብር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ላይ የመስክ ምልከታ ተካሂዷል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮው ክፍተኛ ባለሙያዎችና የፕሮግራሙ አስተባባሪዎች እንዲሁም የቴክንክ ኮሚቴዎች በመሬት አያያዝና አስተዳደር የአየር ንብረት ማሻሻያ (CALM) ፕሮግራም በዳውሮ፣ በኮንታ እና በካፋ ዞኖች በንዑስ ተፋሰስ አስተዳደርና ልማት እና የገጠር መሬት ምዝገባና አስተዳደር ስራዎችን…

Read More

በ2016 በጀት ዓመት የተሟላ የግብር ህግ ማስከበር ስራ በቅንጅት ይሰራል

ወ/ሮ ትዕግስት በላይ ወ/ሮ ትዕግስት በላይ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊና የግብር ህግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ ማህበረሰቡ ግብይት በምፈፅምበት ወቅት ደረሰኝ በመቀበል የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የክልሉን ህዝቦች ያደረ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ ነው ክልሉ የተመሰረተው ያሉት ዘርፍ ኃላፊዋ የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ደግሞ ክልሉ ከሚያመነጨው ኢኮኖሚ ግብርን…

Read More

በክልሉ በ2016 የበጋ መስኖ ልማት 11 ሺህ ሄክታር ማሳ በስንዴ ይሸፈናል።

በክልሉ በአርሶአደር እና በባለሀብቶች እንዲሁም በተለያዩ አደረጃጀቶችን በማሳተፍ የተሻለ ምርት ለማምረት እየተሰራ እንደሆነ ታዉቋል። በ2016 በጀት ዓመት በ11 ሺህ ሄክታር መሬት የበጋ ስንዴ ለማምረት እቅድ ተይዞ የዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን በዞኖች የቴክኒክ ኮሚቴ ተዋቅሮ የማሳ ልየታና የዝግጅት ስራዎች መጀመሩ ተገልጿል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ለ6 ፖሊስ መኮንኖች የረዳት ኮሚሽነርነት የማዕረግ ዕድገት ተሰጣቸዉ።

የማዕረግ ዕድገት የተሰጣቸውም1ኛ ረዳት ኮሚሽነር ከበደ ደበበ2ኛ ረዳት ኮሚሽነር ዶክተር ካሣ3ኛ ረዳት ኮሚሽነር በዛብህ ገዝሙ4ኛ ረዳት ኮሚሽነር ገበራ ገብሬ5ኛ ረዳት ኮሚሽነር ኃይሌ ጪማ እና6ኛ ረዳት ኮሚሽነር ኃብታሙ መላኩ ናቸው የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ እና የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰብስቤ ሻዎኖ ለ6 ረዳት ኮሚሽነሮች ማዕረግ አልብሰዋል። ለበርካታ ዓመታት በፖሊስ ተቋም መስራታቸውንና በሠሩባቸው ውጤታማ…

Read More

የበጀት ዓመቱ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ና የሌማት ትሩፋት ስራዎች ንቅናቄ መድረክ ተጀመረ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ክልላዊ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ስራዎች የ2015 አፈጻጸምና የ2016 ዕቅድ የንቅናቄ እንዲሁ የሌማት ትሩፋት ተግባራት አፈጻጸም የሚገመግም መድረክ በቦንጋ እየተካሄደ ይገኛል። ክልሉ ለእርሻ ስራ አመቺ የሆነ የአየር ፀባይና ሊለማ የሚችል ሰፊ መሬት እንዲሁም በቂ የከርሰምድርና ገጸምድር የውሃ ሀብት ያለው መሆኑን የገለጹት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ…

Read More

በክልሉ የምርጥ ዘር አቅርቦት ችግር ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ ነው:- አቶ ማስረሻ በላቸው።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸዉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ድርጅት የዘር ብዝዬት ስራን በኮንታ ዞን በይፋ አስጀምረዋል። ድርጅቱ በኮንታ ዞን ኮይሻ ወረዳ በቡላ ሀማኮ ቀበሌ በ10 ሄክታር ማሳ የማሾና የቦለቄ መስራች ዘር በማባዛት ነው ስራውን የጀመረው። ድርጅቱ በክልሉ የመስተዳድር ምክር ቤት…

Read More

በኮንታ ዞን በአልሚ ባለሀብቶች እየለማ የሚገኘው የግብርና ስራ ተስፋ ሰጪ ነው ሲሉ አቶ ማስረሻ በላቸው ተናገሩ።

በኮንታ ዞን በግል ባለሀብት እየለማ የሚገኘውን የግብርና ስራዎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ምልከታ አድርገዋል ። በኮንታ ዞን በኮንታ ኮይሻ ወረዳ ኦሽካ ዴንቻ ቀበሌ በግል ባለሀብቱ እየለማ የሚገኘው የግብርና ልማት ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትለል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ተናግረዋል ። የአቶ ግርማ እሸቴ የቡና ልማት እና የፍራፍሬ…

Read More