Trendings

ፕሬዝዳንቱ ለሁለቱ ምክር ቤቶች ያቀረቡት ንግግር የፌደራል መንግስት ዓመታዊ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን ያመላከተ ነው

በፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ለሁለቱ ምክር ቤቶች የቀረበው የመክፈቻ ንግግር የፌደራል መንግሥትን የ2018 ዋና ዋና ሀገራዊ የልማት ዕቅዶችና የትኩረት አቅጣጫዎችን ያመላከተ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ገለጹ። 6ኛው ዙር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመን አንደኛ መደበኛ ስብሰባ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ለሁለቱ ምክር ቤቶች ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር…

Read More

ለክልሎች የተንቀሳቃሽ ክሊኒክ አምቡላንሶች ድጋፍ ተደረገ

ጤና ሚኒስቴር ለዘጠኝ ክልሎች 450 ሚሊየን ብር የሚያወጡ የተንቀሳቃሽ ክሊኒክ አምቡላንሶች ድጋፍ አድርጓል። የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ÷ አምቡላንሶቹ ከጃፓን መንግስት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ መገዛታቸውን ተናግረዋል፡፡ ድጋፉ በተለያዩ አካባቢዎች በዘርፉ የሚስተዋሉ መጠነ ሰፊ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚያግዝ ነው የገለጹት፡፡ በተለይም የእናቶችና ጨቅላ ሕጻናት ጤና አገልግሎት ጥራት እና ተደራሽነትን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚያስችሉ አስረድተዋል፡፡ የአምቡላንስ ድጋፉ በእናቶችና…

Read More

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ግብይት ሥርዓት በዛሬው ዕለት ተጀመረ

በማስጀመሪያ መርሐ-ግብሩ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ጨምሮ፣ የሀገራት አምባሳደሮችና ሌሎችም ሚኒስትሮች ተግኝተዋል። የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ፤ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ግብይት የኢትዮጵያ ወጪ ንግድ ከማሳለጥ ረገድ ሚናው የጎላ ነው። ከዚህ ባለፈም የኢትዮጵያን የንግድ ዘርፍ መስፈንጠር ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አስገንዝበዋል፡፡ በተለይ በእቃዎች ዋጋ ተመን (ታሪፍ) ላይ ስምምነት ተደርሶ፣ ዛሬ የመጀመሪያውን ጭነት…

Read More

በሸካ ዞን በዘንድሮ መኸር እርሻ 3ሺህ 122 ሄክታር መሬት በሩዝ ምርት እየለማ ነው

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሸካ ዞን በዘንድሮ 2017/18 መኸር እርሻ 3ሺህ 122 ሄክታር መሬት በሩዝ ምርት እየለማ እንደሚገኝ የዞኑ ግብርና፣አከባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ መምሪያ አስታውቀዋል ። የዞኑ ግብርና፣አከባቢ ጥበቃና የህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ አዕምሮ ደሳለኝ ፤በዞኑ በመኸር ወቅቶች በሩዝ ምርት እርሻ ሥራ ከጊዜ ወደ ጊዜ የማሳ ሽፋን፣የምርታማነት ዕድገትና የአርሶ አደሮች ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን…

Read More

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ1ኛ መደበኛ ስብሰባው የቀረበውን የድጋፍ ሞሽን በሙሉ ድምጽ አጸደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 1ኛ መደበኛ ስብሰባው ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ መስከረም 26/2018 ዓ.ም ለሁለቱ ምክር ቤቶች ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ የቀረበን የድጋፍ ሞሽን በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ስብሰባው በሁለት አጀንዳዎች ላይ ውይይት አካሂዷል። በዚህም ምክር ቤቱ በመጀመሪያ አጀንዳም በ4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ…

Read More

እንደሀገር ብሎም እንደክልል በከተሞች የነዋሪ ቁጥር በፍጥነት እያደገ በመምጣቱ የከተሞች ዕድገት የህዝብን ዕድገትና ፍላጎትን ታሳቢ ያደረገ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎች በመሰራት ላይ ይገኛሉ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በክልሉ ያሉ ከተሞችን ውብ፣ ጽዱና ለዜጎች ምቹ ከማድረግ አንጻር ዘርፌ ብዙ ተግባራትን ያከናውናል። ከነዚህም አንዱ በቢሮው የመሬት ልማት ማኔጅመንት ዘርፍ የሚሰሩ ስራዎች ናቸው። ዘርፉ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል በዋናነት ለአልሚዎች ጥራት ያለውንና ለተለያዩ አገልግሎት የሚሆን መሬትን በበቂ ሁኔታ ማዘጋጀት፣ የተዘጋጀውን መሬት በተቀመጠው አሠራር ስርዓት አዋጅና ደንብ መሠረት…

Read More

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀዳሚ አየር ኃይል የመገንባት ውጥን ይዛ እየሰራች ነው – ሌ/ጄነራል ይልማ መርዳሳ

ኢትዮጵያ በ2022 ዓ.ም ከአፍሪካ ቀዳሚ አየር ኃይል የመገንባት ውጥን ይዛ እየሰራች ነው አሉ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጄነራል ይልማ መርዳሳ። የኢፌዴሪ አየር ኃይል ለአካዳሚው ያሰለጠናቸውን መሠረታዊ ወታደሮች በዛሬው ዕለት አስመርቋል። ሌ/ጄነራል ይልማ መርዳሳ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ተመራቂዎች ለላቀ ግዳጅና አፈፃፀም ራሳቸውን ማዘጋጀት ይኖርባችኋል፡፡ ኢትዮጵያ የያዘችውን ከአፍሪካ ቀዳሚ አየር ኃይል የመገንባት ውጥን የሚመጥን ቴክኖሎጂና የሰው ኃይል…

Read More

የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የባለሙያዎችን ክህሎት በስልጠና መገንባት ወሳኝ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከክልሉ የምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ (FSRP) ፕሮግራም ጋር በመተባበር የበጋ መስኖ ስንዴ አመራረት ፓኬጅ ላይ ከዞንና ከወረዳ ለተወጣጡ ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ይገኛል፡፡ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትልና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ክንፉ ስልጠናውን ባስጀመሩበት ወቅት፣ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የባለሙያዎችን ክህሎት በስልጠና መገንባት ወሳኝ መሆኑ ተናግረዋል፡፡…

Read More

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በጭዳ ከተማ የአቅሜ ደካማ መኖሪያ ቤት ግንባታ አስጀመረ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በኮንታ ዞን በምትገኘው ጭዳ ከተማ፣ አቅመ ደካማና ጠያቂ ለሌላቸው እናት የመኖሪያ ቤት ግንባታ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጀመረ። ይህ የክረምት ወራት የበጎ አድራጎት ሥራ የክልሉ መንግሥት አቅመ ደካሞችን ለመደገፍ የያዘው ሰፊ መርኃ ግብር አካል መሆኑ ተገልጿል። የቤቱ ግንባታ የተጀመረላቸው ወ/ሮ በየነች መኮንን፣ በከተማው ውስጥ በችግርና ያለረዳት በደሳሳ…

Read More