Trendings

ሁለንተናዊ ማህበራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት አመራር ቁርጠኝነት መጠናከር አለበት – አቶ ፍቅሬ አማን

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ የ2018 በጀት ዓመት ክልላዊ የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አፈጻጸም በቦንጋ ከተማ እየገመገመ ይገኛል። በመድረኩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን፥የዜጎችን ሁለንተናዊ ማህበራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት በየደረጃው የሚገኘው አመራር ቁርጠኝነት መጠናከር አለበት ብለዋል። ባለፉት ጊዜ በቅንጅት በተሰራው ውጤታማ ሥራ የክልሉ የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና አፈጻጸም…

Read More

የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት የስድስት ወራት አፈጻጸም ግምገማ እየተደረገ ነዉ።

የክልሉ የአስፈጻሚ ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ ሴክተር መ/ቤቶች ግምገማ መድረክ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ሶስተኛ ቀኑን በያዘው የግምገማ መድረክ ላይ የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ ባስተላለፉት መልዕክት በ2018 በጀት ዓመት ሁለም ተቋማት በተናበበና በተቀናጀ ዕቅድ ወደ ተግባር እንዲገቡ መደረጉንና አፈፃፀሙንም ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ገልፀዋል። የተቋማት ዋና ዋና የልማት ዕቅድ የትኩረት…

Read More

የኢትዮጵያ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግርን በአጭር ጊዜ የሚያሳልጥ ወሳኝ እርምጃ ነው – ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ

የኢትዮጵያ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግርን በአጭር ጊዜ የሚያሳልጥ ወሳኝ እርምጃ ነው – ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የኢትዮጵያ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግርን በአጭር ጊዜ የሚያሳልጥ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ። ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮችና የፌደሬሽን ምክር ቤት 5ኛ የሥራ ዘመን የጋራ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የፌዴራል መንግስትን የ2018 ዓ.ም…

Read More

ከተቋቋመ በአንድ ወር ውስጥ 8 ሺህ ቶን ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ ሸኝቷል፦ የቦንጋ ምርት ጥራትና ሴርትፊኬሽን ማዕከል

ቡና ብዙ ተጠቃሚ ካላቸው እና ብዙ ጥቅም ላይ ከሚውሉ መካከል አንዱ ነው፡፡ አሃዛዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ከሆነ በዓለም ላይ በቀን በጣም ብዙ የሚባል ሲኒ ቡና ተጠቃሚ እንደለው ነው የሚነገረው፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያም አሁን አሁን በየቦታው የጀበና ቡና ቤቶች ተከፍተው ይገኛሉ፡፡ ይህም ስራ ዕድል መፍጠሩ አንዱ ነገር ሆኖ ሳለ ከዚህም በተጨማሪ ቡና በሀገር ደረጃ ምን ያህል ተጠቃሚ እንደለው…

Read More

የዕቅድ ክትትልና ግምገማ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመን ያለመ የሥራ ጉብኝት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ተጀመረdcs

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የእቅድ አፈጻጸምና የልማት ፕሮጀክቶች አስተዳደርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመን እና ለማጠናከር ያለመ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ በፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የተመራ የፌደራል ልዑክ ቦንጋ ከተማ ገብቷል። የልዑካኑ ጉብኝት ዋና ዓላማ የክልሉን የልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ግልጽ፣ ቀልጣፋና ተጠያቂነት የሰፈነበት ለማድረግ የሚያስችል ዘመናዊ የዲጂታል እቅድ ክትትልና ግምገማ ስርዓትን በተግባር ላይ ለማዋል…

Read More

የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የአገሪቱን ዘላቂ ዕድገትና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን ማዕከል ባደረገ መልኩ እየተገነባ ነው

የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የአገሪቱን ዘላቂ ዕድገትና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን ማዕከል ባደረገ መልኩ እየተገነባ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ካለፈው ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን ድረስ የሚቆየውን የ”ኢትዮጵያ ታምርት” ኤክስፖ በይፋ መክፈታቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ በዘንድሮው “ኢትዮጵያ ታምርት” ኤክስፖ ላይ የሀገራዊ ርዕያችንን ተጨባጭ ስኬት መመልከት…

Read More

ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ ለከተሞች የተለያዩ ደረጃ እና ዓይነት ያላቸው 86  ፕላኖች ተዘጋጅተዋል-የክልሉ ከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት

የከተማ ትልቁ ሀብት መሬት ነው።የከተሞች ውስን ሀብት የሆነው የከተማ መሬትን በአግባቡ ማስተዳደር ከተማን የሚመጥን ፕላን ማዘጋጀት ያስፈልጋል። የከተማ ፕላን የአንድን ከተማ እና የአካባቢውን የወደፊት ዕድገት የህዝቡን ጥቅም እና የከተሞችን እድገት መሰረት በማድረግ እንዲመራ ተደረጎ የሚዘጋጅ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ሲሆን በይዘት ደረጃ የከተማውን መሬት አጠቃቀም፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ታሪካዊ፣ የፊዚካላዊና ሌሎች ጉዳዮችን ያካትታል፡፡ ከተሞች በፕላን ሲመሩ ለከተማው…

Read More

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ነው

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ በኢትዮጵያ በተለያዩ ከተሞች እየተከበረ ይገኛል። ዘንድሮ ቀኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ114ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ “ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል” በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራል። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ ከተማ አስተዳድሮች በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ እንደሚገኝ ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Read More

የ24 ዓመቱ የማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤት አትሌት ኬልቪን ኪፕቱም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ::

የ24 ዓመቱ የማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤት ኬንያዊው አትሌት ኬልቪን ኪፕቱም በመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የዓለም አትሌቲክስ አስታወቀ። ኪፕቱም ባለፈው ጥቅምት ወር ቺካጎ ውስጥ በተደረገ የማራቶን ውድድር 2:00:35 በሆነ ሰዓት በመግባት የዓለም ክብረ ወሰን መስበሩ ይታወሳል። ይኸው ክብረ ወሰን ባለፈው ሳምንት መጽደቁም ይታወቃል። አትሌቱ እና ሩዋንዳዊ አሠልጣኙ ጌርቫይስ ሐኪዚማና ሕይወታቸው ያለፈው ኤልዶሬት ካፕታጋት በተባለ…

Read More

በ2017 በጀት ዓመት በማህበራዊና ኢኮኖሚ ዘርፎች ስኬት የተመዘገበበት መሆኑን አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ ተናገሩ ፡፡

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በታርጫ ከተማ ተጀምሯል ፡፡ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወንድሙ ኩርታ በጉባኤው መክፈቻ እንደተናገሩት ባለፉት የበጀት ዓመት ምክርቤቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠዉን ሀላፊነት ለመወጣት የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። ምክር ቤቱ በህገ-መንግስትና በምክር ቤቱ የአሰራርና የአባላት ስነ-ምግባር ደንብ የተሰጠዉን ተግባርና በበጀት…

Read More