ሕዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ ዕቅድን በአግባቡ መተግበር እንደሚገባ ተገለጸ
አማራ ክልልን ከነበረበት ሁኔታ የሚያሻግርና ሕዝብን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሥራ ለመተግበር ዕቅድን በኃላፊነት መፈጸም እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አስገነዘቡ፡፡ የአማራ ክልል ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በተገኙበት የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡ በመድረኩም ክልሉን በተለያየ መስክ ለማሳደግና ከ2018 እስከ 2022 ዓ.ም የሚተገበር ፍኖተ-ካርታ ተዘጋጅቶ በየደረጃው ላለው አመራር…
