Trendings

Getenesh Gebeyehu

ትውልድ ነቅቶ ከመባላት በመውጣት ሃብቱን ማልማትና ከልመና መውጣት ይገባዋል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ትውልድ ልመናን እየተቀባበለ መሄድ የለበትም የሚል ፅኑ እምነት ይዘን ፀጋዎቻችንን በማልማት ሀገርን ወደ ብልጽግና ለማሸጋገር እየሠራን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ “ኢትዮጵያ በባሌ ምድር ያለውን የተፈጥሮ ፀጋ ይዛ ለምን ለማኝ ሆነች የሚለውን ጥያቄ መመለስ አልቻልኩም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያውያን ከኋላ ጋር ያለን ፀብ ወደፊት መራመድ እንዳንችል በእጅጉ ይዞናል፤ ወደኋላ ማየት ያለብን ለትምህርት…

Read More

በክልሉ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም እየተሰሩ ያሉ ተግባራት በዘርፉ ምርታማነት ለማሳደግ ሚናው ከፍ ያለ መሆኑን አስተያየት ሰጪዎች ተናገሩ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የሚደገፍ የጎጀብ እና ታርጫ ምርምር ንዑስ ጣቢያዎች የመስኖ ጥናትና ዲዛይን ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ በኃላ በኢንስቲትዩቱ ግቢ እየታሰሩ ያሉ ተግባራትን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ የኢንስቲትዩቱን ግቢ የተሰሩ ለምርምር የሚያግዙ ስራዎችን የተመለከቱት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አስተያየታቸውን ስጥተዋል ። በምርምር ኢንስቲትዩት ግቢ እየተሰሩ ያሉ…

Read More

የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ከምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም(FSRP) ጋር በመሆን በግብርናው ዘርፍ በተሰሩ ስራዎች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑ ተገለጸ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት በምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የሚደገፍ የጎጀብ እና ታርጫ ምርምር ንዑስ ጣቢያዎች የመስኖ ጥናትና ዲዛይን ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ በቦንጋ አካሂደዋል። በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል አለሙ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) ከተቋሙ ጋር በመቀናጀት በክልሉ በሚገኙ…

Read More

በዩኒሴፍ ፕሮግራም ድጋፍ የተሰሩ ዉጤታማ ተግባራትን አጠናክሮ ለማስቀጠል ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በ2017 በጀት ዓመት በዩኒሴፍ ድጋፍ የተሰሩ ፕሮጄክቶች የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል፡፡ በፕሮግራሙ የታቀፉ የ8 ሴክተሮች አፈጻጸም ሪፖርት ቀርበው ግምገማ የተደረገባቸዉ ሲሆን በቀጣይ መስተካከል የሚገባቸው ሀሳቦች ላይ ዉይይት ተደርጎ ከመግባባትም ተደርሷል፡፡ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ እንዳሉት፤በ2017 በጀት ዓመት በክልሉ በዩኒሴፍ ፕሮግራም ገንዘብ ድጋፍ በተሰሩ…

Read More

መንግስት የግል ኢንቨስትመንት ተሳትፎን ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

መንግስት እያደገ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ የግል ኢንቨስትመንት ተሳትፎን ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ ገለፁ። በአቶ አህመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ድርጅት ዳይሬክተር ማክታር ዲዮፕ እንዲሁም ከባለብዙ ወገን ኢንቨስትመንት ዋስትና ኤጀንሲ ስራ አስፈፃሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሂሮሺ ማታኖ ጋር ተወያይቷል። ውይይቱ በዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ ከሚገኘው የዓለም አቀፉ…

Read More

የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት በሚፋጠንበት አግባብ ላይ ውይይት ተደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኒኮዚ አዌላ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸው ወቅትም፥ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል እንድትሆን እየተደረገ ባለው ጥረት ላይ መክረዋል። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል መሆኗ ለዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የጎላ ሚና እንዳለውም ተጠቁሟል። በመሆኑም በፈረንጆቹ መጋቢት 2026 በካሜሩን ያውንዴ በሚካሄደው 14ኛው የዓለም…

Read More

የክልሉ መንገዶች ባለስልጣን የዋና የፕሮጀክቶች አፈጻጸምን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ ገምግሟል

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንገዶች ባለስልጣን ዋና መስሪያ ቤት እየተሰሩ ያሉ የመንገድ ጥገናና ድልድይ ፕሮጀክቶች ያሉበት ደረጃ ገምግመው ቀጣይ በሚጠናቀቁበት ጉዳዮች ላይ ከአማካሪዎች፣ ተቋራጮችና ባለድርሻ አካላት ጋር መክረዋል። በ2017 በጀት ዓመት በግልፅ ጨረታ አሸንፎ ወደ ስራ የገቡት አራት የስራ ተቋራጮች እና ሁለት አማካሪ ድርጅቶች እየተሰሩ ያሉ የኮቾ፣ኡሜ እና መንሳ ድልድዮች እንዲሁም ዳካ-ሳይለም ሎት 2…

Read More

በአንደኛ ዙር የበጋ መስኖ በስንዴና ሆልቲካልቸር ከ10 ሚሊየን በላይ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች መንግስት ግብርና ቢሮ በምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም በጀት ድጋፍ የተዘጋጀ የበጋ መስኖ ስንዴ እና መደበኛ መስኖ አመራረት ፓኬጅ አሰልጣኞች ሥልጠና በሚዛን አማን እየተሰጠ ነው። በክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የእርሻና ሆልቲካልቸር ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ክንፉ እንደገለጹት ግብርና የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ሆኖ እንደቀጠለ ተናግረዋል ። የግብርና ምርትና ምርታማነት ለውጥ አምጥቶ ሀገርን ከመመገብ…

Read More

የኑሮ ውድነት ፣ስራ ዕድል ፈጠራና ከተረጅነት ለመላቀቅ የተያዙ ግቦች በተሟላ መልኩ እንዲፈጸሙ የባለድርሻ ተቋማት ቅንጅት ሊጠናከር እንደሚገባ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለጹ

የብልጽግና ፓርቲ 2018 በጀት ዓመት የሩብ ዓመት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ዛሬም ቀጥሎ በመካሄድ ላይ ነው። በዛሬው መድረክም በፓርቲና በመንግሥት ቅንጅት የሚሰሩ ስራዎች አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት እየተካሄደ ሲሆን የስራ ዕድል ፈጠራ ፣ኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የተሰሩ ስራዎችና የተገኙ ውጤቶች እንዲሁም ከተረጅነት የመላቀቅ ግቦች የውይይቱ አጀንዳዎች ናቸው። የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ እንዳሉት፤…

Read More

የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያን የለውጥ አጀንዳ እንደሚደግፍ ገለጸ

የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያን የለውጥ አጀንዳ በበጀት ጭምር እንደሚደግፍ የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ ፕሬዚዳንት ሲዲ ኦልድ ታህ(ዶ/ር) ገለጹ። የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ ከአዲሱ የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ ፕሬዚዳንት ሲዲ ኦልድ ታህ(ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። የዓለም ባንክ እና አይ ኤም ኤፍ አመታዊ ስብሰባዎች ጎን ለጎን ነው የሁለትዮሽ ትብብርን ለማጠናከር ሁለቱ ወገኖች ውይይቱን ያደረጉት። አቶ አህመድ ሺዴ…

Read More