የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባዔና የምክክር መድረክ ተካሄደ

የክልሉ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት የ6 ወራት ጠቅላላ ጉባዔና የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሄደ። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ደስታ ጥላሁን ፓለቲካ ፓርቲዎች በአገራችን ፓለቲካዊ፥ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ንቁ ተሳታፊ በመሆን በህግ የበላይነት እና በዜጎች ደህንነት በጋራ ጉዳዮች ላይ በጋራ በመነጋገር ችግሮችን የመፍታት…

Read More

የሚያለዩንና የሚያናቁሩንን ነጠላ ትርክቶች በመተው የጋራ የሚያደርጉንና ገዥ ትርክቶችን ማጽናት ይገባል ። ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፌ መሀመድ

“ሕብረብሔራዊ ወንድማማችነት ለዘላቂ ሰላም እና ሁለንተናዊ ብልጽግና ” በሚል መሪ ሀሳብ በቦንጋ ከተማ የተካሄደው ህዝባዊ ውይይት ተጠናቋል። በቦንጋ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ ውይይቶች ከተሳታፊዎች አስተያየት እና ጥያቄዎች ቀርበዋል። ከቦንጋ ከተማና ከዙሪያ ወረዳዎች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በዞኑ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ሆነው የሰነበቱ ምላሽ እያገኙ መምጣታቸውን ተናግረዋል ። ከለውጡ ማግስት በዞኑ እየተስተዋሉ ያሉ ጅምር የልማት ስራዎች በዘላቂነት ለፍጻሜ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾና የኢፌዲሪ ገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ሀዋሳ ከተማ ገቡ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾና የኢፌዲሪ ገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ በነገው ዕለት በሲዳማ ክልል “ህብረብሔራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ለዘላቂ ሰላምና ሁለንተናዊ ብልፅግና” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደውን ህዝባዊ የውይይት መድረክ ለመምራት ሀዋሳ ከተማ ገብተዋል። እንግዶቹ ሀዋሳ አለም አቀፍ አየር ማረፍያ ሲደርሱ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም…

Read More

የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ::

አዲስ አበባ፦ በበጀት ዓመቱ ባለፉት ሰባት ወራት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር አስታወቀ። አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቶን ገቢና ወጪ ጭነት እንዲሁም ከ115 ሺህ በላይ መንገደኞች ማጓጓዙን ማኅበሩ ጨምሮ ገልጿል፡፡ በማኅበሩ ከፍተኛ የእቅድና የፕሮግራም አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ፍስሐ መብራህቶም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት…

Read More

በዝናብ ጥገኝነት ታሪክ ይሆን ይሁን? ተስፋ ሰጪ የመስኖ ልማት ስራዎች በክልላችን!

መስኖ ማለት የገፀ-ምድር ወይም የከርሰ ምድር ውኃን በሰው ሰራሽ መንገድ በባህላዊ ወይም ዘመናዊ አሠራር በመጠቀም ወደ እርሻ መሬት በማድረስ ዝናብ ሳይጠበቅ ሰብልን ፣ የጓሮ አትክልትን ወይም ፍራፍሬ ተክሎችን የማልማት መንገድ ነው፡፡ የዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚዘረዝሩት ከሆነና በተግባርም እንደተረጋገጠው መስኖ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ በተለይ በረሃማ በሆኑ አካባቢዎችና የዝናብ እጥረት በሚኖርባቸው ወቅቶች የመስኖ ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው፡፡ የመስኖ…

Read More

ሰላም እና ልማት ለኅብረተሰቡ አስፈላጊ ስለሆኑ አንዱ ያለሌላው ሊሳካ አይችልም፡- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ::

በአማራ ክልል የልማት ሥራዎች ዙሪያ የሚመክር የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ውይይት በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው። በምክክር ሂደቱ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ እና ሌሎችም የፌዴራል መንግሥት አመራሮች ተገኝተዋል። የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ወደ ክልሉ ለመጡ…

Read More

በክልሉ በዘንድሮ በበልግ እርሻ ከ3 መቶ 20 ሺህ ሄክታር መሬት በማረስ 11.9 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዷል – አቶ ማስረሻ በላቸው::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ የ2015/16 ምርት ዘመን የበልግ ተግባር አፈፃፀም ግምገማና የ2016/17 ምርት ዘመን የበልግ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በንቅናቄ መድረኩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት እንደ ክልል ተደራጅተን ወደ ስራ ከገባን ጊዜ ጀምሮ…

Read More

የ24 ዓመቱ የማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤት አትሌት ኬልቪን ኪፕቱም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ::

የ24 ዓመቱ የማራቶን ክብረ ወሰን ባለቤት ኬንያዊው አትሌት ኬልቪን ኪፕቱም በመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የዓለም አትሌቲክስ አስታወቀ። ኪፕቱም ባለፈው ጥቅምት ወር ቺካጎ ውስጥ በተደረገ የማራቶን ውድድር 2:00:35 በሆነ ሰዓት በመግባት የዓለም ክብረ ወሰን መስበሩ ይታወሳል። ይኸው ክብረ ወሰን ባለፈው ሳምንት መጽደቁም ይታወቃል። አትሌቱ እና ሩዋንዳዊ አሠልጣኙ ጌርቫይስ ሐኪዚማና ሕይወታቸው ያለፈው ኤልዶሬት ካፕታጋት በተባለ…

Read More

ያለ አገልግሎት ለዘመናት በኖረው ስፍራ ዘመን የማይሽረው ሥራ ተሠርቷል፦ ከንቲባ አዳነች::

ያለምንም አገልግሎት ለዘመናት በኖረው ስፍራ ዘመን የማይሽረው ሥራ ሠርተናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ፒያሳ የተገነባውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ መርቀዋል፡፡ ምረቃውን ተከትሎም ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባደረጉት ንግግር÷ ያለምንም አገልግሎት ለዘመናት በኖረው ስፍራ ዘመን የማይሽረው ሥራ እንዲከናወንበት መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡ ለዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)…

Read More

የዓድዋ ድል መታሰቢያው እስካሁን ባለመገንባቱ ያስቆጫል፦-ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ::

የዓድዋ ድል ከሀገርና አኅጉር ተሻግሮ በዓለም የተስተጋባ አኩሪ ድላችን ቢሆንም ይህን በአንድ ቦታ በአግባቡ የሚገልጽ የዓድዋ ድል መታሰቢያ አለመገንባቱ የሚያስቆጭ ነው ሲሉ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ገለጹ፡፡ ፕሬዚዳንት ሣኅወርቅ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ የዓድዋ ድል መታሰቢያ የእኛ ብቻ ሳይሆን ለነጻነት፣ ለሕዝቦች እኩልነት ተስፋን የሰጠ ድል ነው ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ ይህን ድል ይዘን እስካሁን ታሪካችንን የሚመጥን…

Read More