በክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተመሩ የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አባላት የገብረፃዲቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታልን ጎበኙ::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ በተከበሩ ወንድሙ ኩርታ የተመራው የም/ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ አባላት ቡድን በቦንጋ ከተማ የሚገኘውን የገብረፃዲቅ ሻዎ አጠቃላይ ሆስፒታልን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል። የጉብኝቱ ዓላማ በሆስፒታሉ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ምልከታ በማድረግ የሚስተዋለውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በቅንጅት በመፍታት ለተሻለ አገልግሎት ምቹ ሁኔታን መፍጠር ላይ ያተኮረ እንደሆነ አፈ ጉባኤው ገልጸዋል። በጉብኝቱ ወቅት…

Read More

ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታና የንቅናቄ ስራዎቻችንን አጠናክሮ በማስቀጠል ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በተናበበ መልኩ መሰራት ይገባል፦ አቶ ነጋ አበራ::

ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታና የንቅናቄ ስራዎቻንን አጠናክሮ በማስቀጠል ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በተናበበ መልኩ መሰራት ይገባል ሲሉ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አቶ ነጋ አበራ ገለጹ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የ2016 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የቀጣይ ወራት የንቅናቄ መድረክ…

Read More

የብሪክስ ጥምረት የዲፕሎማሲ ግንኙነትን ለማስፋትና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ለማሳደግ ይረዳል – አምባሳደር ዲና

የብሪክስ ጥምረት ኢትዮጵያ በዓለም የዲፕሎማሲ ግንኙነት ዕድሎችን እንድታሰፋና ኢኮኖሚያዊ ትብብሯን እንድታጠናከር ያደርጋል ሲሉ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለጹ። በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት የደቡብ ደቡብ ትብብርን በማስተዋወቅ ኢትዮጵያ በብሪክስ አባልነት የሚኖራትን ሚና፣ ዕድልና ቀጣይ ስራ የሚዳስስ የምክክር መድረክ ተካሂዷል። አምባሳደር ዲና እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ በብሪክስ አባልነት…

Read More

ባለፉት አስር ወራት 301 ሺህ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ወደ ውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት አድርገዋል – የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል::

ባለፉት አስር ወራት 301 ሺህ ዜጎች ክብርና ደህንነታቸውን በጠበቀ መልኩ ወደ ውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ማድረጋቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የተያዘውን በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራትን ዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያ የዘርፉ ባለድርሻ አካላትን በማካተት “ዓመተ-ምርታማነት” በሚል ስያሜ እያንዳንዱ ሥራዎች ወደ ውጤት…

Read More

በሚዛን አማን ከተማ የኮሪደር ልማት እና ፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ እየተካሄደ ነው::

የሚዛን አማን ከተማን ዕድገትና የህዝቡን ፍላጎት ባማከለ መልኩ መልሶ ለማልማት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው። የኮሪደር ልማት ሥራን በከተማ አስተዳደር ደረጃ ማስጀመር እና ጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄን ማስጀመርን ዓለማ ያደረገ ግንዛቤ ማስጨበጫና ምክክር ነው እየተካሄደ ያለው። የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን ከተሞች ቀደም ሲል ደረጃውን ባልጠበቀ ፕላን የተመሠረቱ ሲሆን አሁን ላይ ያለውን…

Read More

መከላከያ ሠራዊቱ ህገ መንግስታዊ ተልዕኮውን በብቃት እየተወጣ ነው – ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ::

መከላከያ ሠራዊቱ ህገ መንግስታዊ ተልዕኮውን በብቃት የመወጣት አኩሪ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ አስታወቁ። ብላቴ የሚገኘው የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል ያሰለጠናቸውን 42ኛ ዙር የኢትዮጵያ ኮርስ መሰረታዊ ኮማንዶ ዛሬ አስመርቋል። በዚህ ወቅት የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ባደረጉት ንግግር፤ መከላከያ ሠራዊት የሀገሪቱን…

Read More

የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመለየትና በመልማት ዘርፉን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ በልዩ ትኩረት እየሠራ ነው፦ የካፋ ዞን ባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ

 ኢትዮጵያ በርካታ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ የቱሪስት መስህቦች ያሏት አገር ነች፡፡ ያሏትን የተፈጥሮ ሀብቶች፣ ታሪካዊ ቅርሶች እንዲሁም የማይዳሰሱ ትውፊቶች በአግባቡ ለመጠቀም ፖሊሲዎችን እንደ አዲስ በመከለስ በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት እየታተረች ትገኛለች፡፡ እነዚህን በርካታ የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎች በአግባቡ በማልማት ከዘርፉ የሚፈለገውን ያህል ኢኮኖሚዊ ጥቅም ማግኘት እንደሚያስፈልግ ይታመናል፡፡ በተለይ ቱሪዝም ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለው ዘርፍ መሆኑ በተደጋጋሚ ይነገራል፡፡ የቱሪዝም…

Read More

በአሁኑ ወቅት አለማችን ክፉኛ እያሳሰቧት ከሚገኙ ጉዳይ ሠው ሠራሽና የተፈጥሮ በሽታዎች ውስጥ የመንገድ ትራፊክ አደጋ አንዱ ሆኖ ይገኛል።

ትንሽ ጥንቃቄ በማድረግ በቀላሉ ሊከለከሉት በሚችሉት በዚህ አደጋየብዙዎች ደጃፍ እየተዘጋ፣ቤተሰብ እየተበተነ፣ለአካል ጉዳት እየተዳረገ ንብረቶች እየወደሙና ሀገራትም ከድህነት ለመላቀቅ የሚያደርጉትን ጥረት እየተጓተተ ነው። እንደዓለም ጤና ድርጅት ሪፖርት መሠረት አደጋው ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሀገሮች በጣም የከፋ ከመሆኑም በላይ እነዚህ ሀገሮች ከፍተኛ ገቢ ያላቸው ሀገሮች ከሚደርስባቸው የሞት አደጋ እጥፍ የሚደርስባቸው ሲሆን በዓለም ከሚደርሰው የሞት አደጋ 90% በእነዚህ…

Read More

በወረዳው እየለማ ያለው የሰሊጥ ምርት ለሌሎች አከባቢዎች ተሞክሮ የሚሆን ነው። አቶ ታመነ በቀለ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የግብርና ቢሮ እና የኮንታ ዞን አመራሮች በኮንታ ኮይሻ ወረዳ የበልግ አዝመራ የተሰሩ የእርሻ ስራዎችን ጉብኝተዋል። በጉብኝታቸውም በበልግ የለማዉ በቆሎ፣ ሰሊጥና ካሳባ ምርት እንዲሁም የአረንጓዴ አሻራ አካል የሆነውን ሙዝ ያለበትን ደረጃ ጎበኝተዋል። በጉብኝት ወቅት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታመነ በቀለ በወረዳ ውስጥ እየተሰሩ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ160 በላይ ትላልቅ የግብርና ኢንቨስትመንት አልሚዎች ተሰማርተዋል::

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ160 በላይ ትላልቅ የግብርና ኢንቨስትመንት አልሚዎች መሰማራታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ገለጹ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት የተገነቡት የቱሪስት መዳረሻዎችም የአካባቢው የሆቴልና ቱሪዝም አገልግሎት ኢንቨስትመንት እንዲነቃቃ በር መክፈታቸውን ተናግረዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ በሁለት ዓመታት ውስጥ የተከናወኑ የሰላምና ልማት ስራዎችን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር…

Read More