አደረጃጀቶች የሕዝብን የሰላምና የልማት ጥያቄ ለመመለስ ፋናወጊ ሆነው ሊንቀሳቀሱ ይገባል፦የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አቶ ፍቃዱ ተሰማ
የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት “የጠንካራ አደረጃጀት ትጋት ለአገራዊ ህልሞቻችን ስኬት” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የነበረውን የ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ አጠናቋል፡፡ በመድረኩ ማጠቃለያና የስራ መመሪያ የሰጡት በሚኒስትር ማዕረግ የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አቶ ፍቃዱ ተሰማ አደረጃጀቶች ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የህዝብ ጥያቄ ለመመለስ እንዲሁም ልማትን በማረጋገጥ ሚናቸውን በመለየት እስከታችኛው የህብረተሰብ…
