ህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠርና ለመቅረፍ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
የሸካ ዞን ህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ቁጥጥር ግብረኃይል የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭትን በተመለከተ በሚስተዋሉ ችግሮችና የመፍትሔ እርምጃዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በቴፒ ከተማ አካሂዷል። የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የግብረኃይሉ ሰብሳቢ አቶ አበበ ማሞ በውይይት መድረኩ እንደገለፁት በዞኑ የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ብሎም በአጠቃላይ ህገ ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠር እና ለመቅረፍ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል።…
