የረዥም ጊዜ ጥያቄ የነበረው “የኔትወርክ አገልግሎት” ምላሽ በማግኘቱ መደሰታቸውን የኮይሻ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ
የዘመናት ጥያቄያቸው የሆነው የኔትወርክ አገልግሎት ምላሽ በማግኘቱ መደሰታቸውን የኮንታ ዞን የኮንታ ኮይሻ ወረዳ የኮይሻ ከተማ ነዋሪዎች ገልፀዋል። የወረዳዉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ያነጋገራቸዉ የከተማዋ ነዋሪዎች በአካባቢው በ21ኛው ክፍሌ ዘመን የኔትወርክና መብራት አገልግሎት አለመኖሩ የዘውትር ጥያቄያቸው እንደነበረና በውስጣቸው ቅሬታ ፈጥሮ የቆየ መሆኑንም ተናግረዋል። በአካባቢው ኔትወርክ ባለመኖሩ የተለያዩ አገልግሎቶች ተጠቃሚ ሳይሆኑ መቆየታቸውን የገለፁት የከተማዋ ነዋሪዎች ለአብነት የባንክ አገልግሎትን…
