“በህዳሴ ግድብ ምክንያት የግብፅ አስዋን ግድብ አንድ ሊትር ውሃ አልቀነሰም”፦ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ እንደገለጹት፣ በህዳሴ ግድብ ምክንያት የግብፅ አስዋን ግድብ አንድ ሊትር ውሃ አልቀነሰም። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ለመረበሽ የሚያስቡ ሰዎች አሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ህዳሴ ግድብ አልቋል በቅርቡ እናስመርቀለን ብለዋል። ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ያለኝ መልዕክት ህዳሴ ለሱዳን፣ ለግብጽ በርከት መሆኑን ነው ብለው፤ በፍፁም ጉዳት አይመጣባችሁም ሲሉ…
