የተቋሙን እቅድ ለማሳካት ሌት ከቀን የምንሰራበት ወቅት ነው ፦ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ
የደምኢህክመ ገቢዎች ቢሮ የበጀት ዓመቱን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው። ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት የገቢ አሰባሰብና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እያደረገ ይገኛል። የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድ በምክክር መድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የታክስ ገቢ መንግስት የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፍላጎት ደረጃ በደረጃ ምላሽ…
