Trendings

በክልሉ የማይነጥፍና ፍትሃዊ የንብረት ግብር ለመሰብሰብ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ግመታና አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል፦ ወ/ሮ ሄለን ደበበ

የኢፌዲሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የሪል ስቴት ልማትና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይትና ግመታ አዋጅ ቁጥር 1357/2017 ላይ የስልጠና መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል፡፡ የስልጠና መድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ የኢፌዲሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስተር ዴኤታ ወ/ሮ ሄለን ደበበ በሪል ፕሮፐርቲ ግመታና ግብይት ወጥነት ያለው ስርዓት ለመዘርጋት እና የከተሞችን የፋይናንስ አቅም ለማሳደግ ገቢ አሰባሰብ ላይ የሚፈለገውን መሠረታዊ…

Read More

አመራሩ የንቅናቄው አጀንዳዎች ፋይዳን በመገንዘብ በላቀ ዝግጁነት መፈጸም ይገባል። አቶ ፍቅሬ አማን

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ በብልጽግና ፓርቲ መሪነት እየተከናወኑ ያሉ የንቅናቄ አጀንዳዎች አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ውይይት በአመያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩን በንግግር የከፈቱት በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን፥ በየደረጃው ያለው አመራር የንቅናቄው አጀንዳዎች ፋይዳን በተገቢው በመገንዘብ በላቀ ዝግጁነት መፈጸም እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል። ዘርፍ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውና ሀገራዊ ፋይዳቸው የላቁ አጀንዳዎች በክልሉ የብልጽግና…

Read More

የኮሪደር ልማት ስራን የተረዱትና የተገበሩት ሞዴል አርሶ አደር አቶ አመነ አምበሎ!

በሸካ ዞን ማሻ ወረዳ የካንጋ ቀበሌ ሞዴል አርሶ-አደር አቶ አመነ አምበሎ ቤታቸውን እና ግቢያቸውን ውብ፣ ጽዱና ለመኖር ምቹ ማድረግ ከአባቶች የወረሱት ባህል ቢሆንም ፤ አሁን መንግስት በሰጠው ትኩረት ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። የቀለም ትምህርትን እስከ ሰባተኛ ክፍል እንደተማሩ የሚናገሩት ሞዴል አርሶ-አደሩ ፤ ስድስት ልጆችን በማስተማር ለውጤት ማብቃታቸውን ተናግረዋል። ባላቸው ዕውቀትና ትጋት ጽዱና ምቹ አካባቢን ከመፍጠር በላይ…

Read More

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 44ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ 1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ከጣሊያን ሪፐብሊክ መንግሥት እና ከዓለም አቀፍ የልማት ማህበር ጋር በተፈረሙ ሁለት የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ ከጣሊያን ሪፐብሊክ መንግስት የተገኘው የ11,500,000 ዩሮ ለአካባቢያዊና አረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት የበጀት ድጋፍ ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል ሲሆን የ16 ዓመት የችሮታ…

Read More

“ፈጠራና ፍጥነት የታከለበት የክህሎት ግንባታ ቀጣይነት ላለው የሥራ እድል ፈጠራና ዋስትና ወሳኝ ነው።”

እንኳን ለዓለም የሠራተኞች ቀን በሰላም አደረሳችሁ! ሀገራችን “በአምራች ኢንዱስትሪዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምቹ የሥራ ሁኔታ ለማህበራዊ ፍትህ” በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ136ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም አቀፍ ሠራተኞች በዓል እያከበረች ትገኛለች። ኢትዮጵያ የዓለም የሠራተኞች ቀንን የምታከብረው የኢንዱስትሪ ሰላምን፣ የሥራ ላይ ደኅንነትንና የሠራተኞችን ክሕሎት ማሳደግን ልዩ ትኩረት በመስጠት ነው፡፡ ወደ ብልጽግና የሚደረገዉ…

Read More

በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በክልሉ መጠነ ሰፊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ አግኝተዋል። አቶ ፍቅሬ አማን

በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅ/ጽ/ቤት የ2017 ዓ/ም የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአማያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የአፈፃፀም ግምገማ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በክልሉ መጠነ ሰፊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል። አቶ ፍቅሬ፥ ፓርቲው በክልሉ የህዝቡን የልማት፣ የመልካም አስተዳደር እና…

Read More

4 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር የተመደበለት የታርጫ ጪዳ ሎት 3 አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ።

የመንገድ ፕሮጀክቱ 64.8 ኪሎሜትር ርዝመት እንዳለውም ተገልጿል ። የታርጫ ጪዳ መንገድ ተጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ተቋርጦ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ መሰንበቱ ይታወሳል። ይህንን ፕሮጀክት ዳግም መጀመሩን በማስመልከትም ንግግር ያደረጉት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የመንገድ ፕሮጀክቱ ተጀምሮ መቋረጡ የአካባቢውን ህብረተሰብ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብሮችን በእጅጉ የጎዳ መሆኑን አስታውሰዋል። የብልጽግና ፓርቲ እና መንግስት ይህንን የህዝቡን የመልካም…

Read More

የሥራና ክህሎት ቢሮ ”ብሩህ አዕምሮዎች፤በክህሎት የበቁ ዜጎች በሚል መሪ ቃል የክህሎት፤ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና ኤግዚቢሽን ቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነዉ።

በውድድርና ኤግዚቢሽን መድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ እንደገለጹት፤ በፊት ለቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚሰጠዉ ትኩረት አነስተኛ በመሆኑ በዘርፉ ውጤት ተገቢዉ ዉጤት ሳይመዘገብ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም የተጀመሩ የተቋማት ግንባታዎች ተጠናቅቀዉ አገልግሎት ባለመስጠታቸውና ተቋማት በሚፈልገው ልክ ቴክኖሎጂ ከማሸጋገር አንጻር የነበራቸው ውስንነቶች ተግዳሮት እንደነበርም አስታውሰዋል። ዋና አፈ-ጉባኤው…

Read More

የዲሪ ማሻ አስፋልት መንገድ ግንባታ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻችንን ይፈታል – የአካባቢው ነዋሪዎች

የዲሪ ማሻ አስፋልት መንገድ ግንባታ ዳግም መጀመሩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን እንደሚፈታላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። የፌደራልና የክልል አመራሮች በተገኙበት ተቋረጦ የነበረው የዲሪ ማሻ አስፋልት መንገድ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ሥራ ትናንት ተጀምሯል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በ2010 ዓ.ም ግንባታው ተጀምሮ በሥራ ተቋራጭ አቅም ማነስ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የዲሪ ማሻ አስፋልት መንገድ ዳግም ሥራ መጀመሩ የአካባቢውን ህብረተሰብ…

Read More

መምህራንን አቅም በመገንባት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው – ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር)

ኢትዮጵያ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል እና የመምህራንን አቅም በመገንባት የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረገች መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለጹ። የትምህርት ሚኒስቴር፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአፍሪካን ብሬይን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ‘በ21ኛው ክፍለ ዘመን አፍሪካን ማስተማርና ማብቃት’ በሚል መሪ ሃሳብ ለሶስት ቀናት የተካሄደው ኢኖቬሽን አፍሪካ 2025 ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በዚህ…

Read More