ኢትዮጵያ በ3ኛው የአፍሪካ-ኢራን ኢኮኖሚያዊ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነው
ኢትዮጵያ በቴህራን እየተካሄደ በሚገኘው 3ኛው የአፍሪካ-ኢራን ኢኮኖሚያዊ ትብብር ጉባኤ እና በኢራን ዓለም አቀፍ ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈች ነው፡፡ ጉባኤው በዋናነት በኢራን እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን የኢንዱስትሪ፣ የንግድና የኢቨስትመንት ትስስር ለማጠናከር አተኩሮ የሚካሄድ ሲሆን፥ በኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ሐሰን ሞዓሊን የተመራ የልዑካን ቡድን በመድረኩ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል። የኢራን ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዝሽኪያን በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፥ ሀገራቸው በጤና፣…
