አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓሉን በተለያዩ መርሃ ግብሮች ሊያከብር ነው
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ ክብረ በዓሉን የእስካሁን ታሪኩንና የወደፊት ተልዕኮውን በሚመጥን መልኩ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ(ዶ/ር) አስታወቁ። ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ የዩኒቨርሲቲውን የራስ ገዝነት የሪፎርም አፈጻጸም እና የ75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ አከበባርን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በወጣው የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ አዋጅ መሰረት…
