Trendings

BLOGS

ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ገቢራዊ ያደረገቻቸው ፕሮጀክቶች ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ ነው፦አፍሪካዊያን ምሁራን

ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ገቢራዊ ያደረገቻቸው ፕሮጀክቶች ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው አፍሪካዊያን ምሁራን ገለጹ። ፕሮጀክቶቹ አፍሪካን እና ቀጣናውን በኢኮኖሚ ለማስተሳሰር ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸውም ምሁራኑ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብ በዜጎች ርብርብ በራስ አቅም ገንብታ አጠናቃለች። የኒውክሌር ኃይልን ለሠላማዊ ግልጋሎት ለማዋል የሚያስችል ፕሮጀክት፣የነዳጅ ማጣሪያ እና የተፈጥሮ ጋዝን፣ግዙፍ የማዳበሪያ…

Read More

በበጀት ዓመቱ በመንገድ መሠረተ ልማት የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ ክልሉ መሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋጂዮ ሳፒ እንዳስታወቁት፣ በአንደኛው የሩብ ዓመት የመንገድ እና ድልድይ ጥገና ስራ ሲከናወን መቆየቱን ጠቅሰው በመንገድ ስራ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የዝግጅት ምዕራፍፎች ላይ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን አስታውቀዋል። በተለይ ለማሽነሪዎች ጥገና ማድረግ ፣በሶስቱም ዲስትሪክቶች ነዳጅ ማስገባት እና ሌሎች ግብዓቶችን በተገቢዉ…

Read More

በመተሳሰብ ላይ የተመሠረተ ልማት ለጋራ ብልፅግና የላቀ ሚና እንዳለው ተጠቆመ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት ከJustice for all PF ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር “ሀገር በቀል እውቀት ለግጭት አፈታትና ዘላቂ ሠላም ግንባታ” በሚል መሪ ሀሳብ የባለድርሻዎች ምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ አካኽዷል። በክልሉ የህዝብ ልህዝብ ትስስር እንዲጎለብት በአርብቶ አደር አካባቢ የምግብ ዋስትና እንዲረጋጥ በመስራትና ሁሉን አካባቢዎች በመንገድ ማስተሳሰር፣ የጋራ ገበያ እንዲኖራቸው በማድረግ ዘላቂ ሠላም በመካከላቸው…

Read More

በክልሉ 26 ሞዴል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል፦ የክልሉ ትምህርት ቢሮ፡፡

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በ1ኛ ሩብ ዓመት በማህበራዊ ዘርፍ ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ በርካታ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት የተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የክልሉን የትምህርት ስራ ውጤታማ ለማድረግ ከክልል እስከ ትምህርት ቤት ድረስ በርካታ የትምህርቱ ሴክተር የንቅናቄ ስራዎች መሰራታቸውን ነው አቶ አልማው የተናገሩት…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፡-

ኢትዮጵያ የተሻለ ቁመና ያላቸውን ተቋማት ፈጥራለች፣ ባለፈው ዓመት የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሀገር ደረጃ 18 ደርሷል፤ በቅርቡ 3 የሚጨመር ሲሆን በዚህ ዓመት 100 ለመድረስ እንሰራለን፣ መሬት፣ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ ንግድ ፍቃድ፣ ግብር ላይ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ ነው፣ የዛሬ 3 ዓመት ኢትዮጵያ ለፓስፖርት ፈላጊ ዜጎች ማቅረብ የምትችለው 270 ሺህ ነበር፤ በዚህ ዓመት 4 ሚሊየን ነው የምታቀርበው፣…

Read More

ምክር ቤቱ የቀረበለትን የድጋፍ ሞሽን አፀደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ መስከረም 26 ቀን 2018 በፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የቀረበውን የ2018 የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫ የድጋፍ ሞሽን አጽድቋል። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በፕሬዚዳንቱ የቀረበውን ሞሽን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ…

Read More

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎችን 100 ለማድረስ እየተሰራ ነው

በዚህ ዓመት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎችን 100 ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምክር ቤት አባላት አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ ላነሱላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፥ በተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበረውን ቅሬታ ለመፍታት በርካታ ውጤታማ ስራዎች…

Read More

ኢትዮጵያ ለመገንጠልም፤ ለመጠቅለልም አትመችም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰላም እና በፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ‎ኢትዮጵያ ለመገንጠልም ለመጠቅለልም አትመችም፤ በሀገር ውስጥ የቆየው የእርስ በእርስ ግጭት መቆም አለበት የሚለው ሀሳብ ቅቡልነት እንዳለው ተናግረዋል። ‎…

Read More

የፍትህ ሥርዓቱን የሚያሻሽሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የፍትህ ሥርዓቱን የሚያሻሽሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት የፍትህ ሥርዓትን በሚመለከት ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ መንግሥት የፍትህ ሥርዓቱን ለማዘመንና ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የፍትህ ሥርዓቱ ነጻነትን…

Read More

የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ቀይ ባህርን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና…

Read More