Trendings

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኅን ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች ላይ በማተኮር ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል፦የዘርፉ ምሁራን

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኅን ሀገራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ አጀንዳዎች ላይ በማተኮር ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ቅድሚያ ሊሰጡ እንደሚገባ የዘርፉ ምሁራን ገለጹ። መገናኛ ብዙኅን የሚያመነጯቸው መረጃዎች ግንዛቤን በመፍጠር፣የሀገር ገጽታ በመገንባት፣ ዕቅድና ፖሊሲዎችን በማስተዋወቅ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ቁልፍ ሚና አላቸው። በዜጎች መካከል የሚንጸባረቁ በብዝኅነት ላይ የተመሰረቱ እሳቤዎች የሚስተናገዱበትን አጀንዳ በመቅረጽም አሰባሳቢ ትርክት ግንባታን በማስተጋባት ብሔራዊ መግባባትን የሚፈጥሩ…

Read More

ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ገቢራዊ ያደረገቻቸው ፕሮጀክቶች ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ ነው፦አፍሪካዊያን ምሁራን

ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን ጨምሮ ገቢራዊ ያደረገቻቸው ፕሮጀክቶች ለቀጣናዊ የኢኮኖሚ ውህደት ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ ነው ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው አፍሪካዊያን ምሁራን ገለጹ። ፕሮጀክቶቹ አፍሪካን እና ቀጣናውን በኢኮኖሚ ለማስተሳሰር ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸውም ምሁራኑ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብ በዜጎች ርብርብ በራስ አቅም ገንብታ አጠናቃለች። የኒውክሌር ኃይልን ለሠላማዊ ግልጋሎት ለማዋል የሚያስችል ፕሮጀክት፣የነዳጅ ማጣሪያ እና የተፈጥሮ ጋዝን፣ግዙፍ የማዳበሪያ…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል፡-

ኢትዮጵያ የተሻለ ቁመና ያላቸውን ተቋማት ፈጥራለች፣ ባለፈው ዓመት የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሀገር ደረጃ 18 ደርሷል፤ በቅርቡ 3 የሚጨመር ሲሆን በዚህ ዓመት 100 ለመድረስ እንሰራለን፣ መሬት፣ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ ንግድ ፍቃድ፣ ግብር ላይ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰሩ ነው፣ የዛሬ 3 ዓመት ኢትዮጵያ ለፓስፖርት ፈላጊ ዜጎች ማቅረብ የምትችለው 270 ሺህ ነበር፤ በዚህ ዓመት 4 ሚሊየን ነው የምታቀርበው፣…

Read More

ምክር ቤቱ የቀረበለትን የድጋፍ ሞሽን አፀደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ መስከረም 26 ቀን 2018 በፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የቀረበውን የ2018 የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫ የድጋፍ ሞሽን አጽድቋል። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። በፕሬዚዳንቱ የቀረበውን ሞሽን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ…

Read More

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎችን 100 ለማድረስ እየተሰራ ነው

በዚህ ዓመት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎችን 100 ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምክር ቤት አባላት አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ ላነሱላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ፥ በተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበረውን ቅሬታ ለመፍታት በርካታ ውጤታማ ስራዎች…

Read More

ኢትዮጵያ ለመገንጠልም፤ ለመጠቅለልም አትመችም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰላም እና በፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ‎ኢትዮጵያ ለመገንጠልም ለመጠቅለልም አትመችም፤ በሀገር ውስጥ የቆየው የእርስ በእርስ ግጭት መቆም አለበት የሚለው ሀሳብ ቅቡልነት እንዳለው ተናግረዋል። ‎…

Read More

የፍትህ ሥርዓቱን የሚያሻሽሉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የፍትህ ሥርዓቱን የሚያሻሽሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት የፍትህ ሥርዓትን በሚመለከት ለተነሳላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ መንግሥት የፍትህ ሥርዓቱን ለማዘመንና ለማሻሻል በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል ብለዋል። የፍትህ ሥርዓቱ ነጻነትን…

Read More

ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና ወስደዋል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ የኮዲንግ ስልጠና መውሰዳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ወቅት ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዲጂታላይዜሽንን በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ወጣቶች በነጻ…

Read More

“በሰላማዊ መንገድ ለሚመጣ ለመታረቅ አይደለም አብሮ ለማስራት ዝግጁ ነን “- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በሠላማዊ መንገድ ለሚመጣ ማንኛውም አካል ለመታረቅ አይደለም አብሮ ለማስራት ዝግጁ ነን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ፤ በሰላማዊ መንገድ ለሚመጣ…

Read More

ማንም አያስቆመንም፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2036 በአፍሪካ ቀዳሚው ኢኮኖሚ ይሆናል – ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2032 በአፍሪካ ሁለተኛው ቀዳሚ ኢኮኖሚ በ2036 ደግሞ ከአፍሪካ ቀዳሚው ኢኮኖሚ እንደሚሆን ተናግረዋል። ይህን ለማሳካት ግን ሁሉም በጋራ መሥራት አለበት ሲሉ ገልፀዋል። አሁን እየሄድንበት ያለው መንገድ ይህን ያመላከተ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ…

Read More