Trendings

በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ107 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል፦ ግብርና ሚኒስቴር

በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በዘር ከተሸፈነው 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት እስካሁን ከ107 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ። የግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ኢሳያስ ለማ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ በርካታ ተግባራት እያተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ በእነዚህ ተግባራትም በግብርናው ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት እየተቻለ መሆኑን ጠቁመው በስንዴ ልማት…

Read More

በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በተለይም በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች የተሻለ ርጥበት ይኖራቸዋል – ኢንስቲትዩቱ

በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በተለይም በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች የተሻለ የርጥበት ሁኔታ እንደሚኖራቸው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ በሚቀጥሉት አስር ቀናት የሚኖረውን የአየር ትንበያ አስመልክቶ ለኢዜአ በላከው መግለጫ በሚቀጥሉት ቀናት የሚኖረው የአየር ሁኔታ ለእርሻ ስራ እንቅስቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው አመላክቷል። ከዚህም ጋር ተያይዞ በምዕራብ እና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚጠበቀው ከባድ ዝናብ ለወቅቱ የእርሻ ስራ…

Read More

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አመራሮች ሹመት አጸደቀ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢን እና የሥራ አመራር አባላትን ሹመት አፅድቋል። 6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4 አመት የስራ ዘመን 36ኛው መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል። ምክር ቤቱ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ አቶ ተስፋዬ ንዋይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾሟል፡፡ እንዲሁም አቶ ተክሊት ይመስል እና ወ/ሮ ነሲም አሊ የምርጫ ቦርድ…

Read More

ረቂቅ በጀቱ 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ መቅረቡ የዋጋ ንረት እንዳይባባስ እና የተረጋጋ ኢኮኖሚ እንዲኖር ያግዛል – ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)

የፌደራል መንግስት በ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ቀርቧል። የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ረቂቅ በጀቱ 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ መቅረቡ የዋጋ ንረት እንዳይባባስ እና የተረጋጋ ኢኮኖሚ እንዲኖር ያግዛል ብለዋል። “ባለፉት ዓመታት አጠቃላይ የበጀት አጠቃቀማችን እና የገቢ አሰባሰብ አቅማችን በጣም እየጨመረ መቷል” ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በተለይም ባለፉት…

Read More

ኢትዮጵያ አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ምርታማነትን እንዲያሳድጉ የፋይናንስና ኢንሹራንስ አገልግሎት እያቀረበች ነው

ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ የሆኑና በአነስተኛ ማሳ የሚያመርቱ አርሶና አርብቶ አደሮችን የፋይናንስ አቅም በማሳደግ ምርትና ምርታማነታቸው እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለፁ። በአነስተኛ ማሳ የሚያመርቱ አርሶአደሮች የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነትና የፋይናስ አቅርቦት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው። የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በውይይቱ መክፈቻ፥ ኢትዮጵያ በ10 ዓመቱ መሪ የልማት…

Read More

እንደ ሀገር ያሉብን አምስት ዋና ዋና ችግሮች ተገቢው ቦታ እንዳንደርስ እያደረጉን ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደ ሀገር ያሉብን አምስት ዋና ዋና ችግሮች ተገቢው ቦታ እንዳንደርስ እያደረጉን መሆኑን ከንግዱ ማኅበረሰብ ወኪሎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የወረስነው ድህነትና ድህነትን ለመውረስ የተዘጋጀ ትውልድ መኖሩ ከአምስቱ ችግሮቻችን የመጀመሪያው ነው ብለው፤ ድህነትን ወርሰን ለማውረስ ያለን ፍላጎትና መሻት ከፍተኛ መሆኑን በካሳንቺስ በተግባር ታይቷል ሲሉም ገልፀዋል። ሁለተኛው ችግር እንደሀገር…

Read More

የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ቀረበ

የፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ቀርቧል፡፡ የረቂቅ በጀቱን መግለጫ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አቅርበው ውይይት እየተካሄደበት ነው። ከ2018 ረቂቅ በጀት 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ እንዲሁም 14 ቢሊዮን ብር ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

ዛሬ ከመላው ኢትዮጵያ ከተወጣጡ የንግዱ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር በዞን፣ በክልል እና ከተሞች ደረጃ ከተካሄዱ ውይይቶች የቀጠለ ውይይት ዛሬ በፌዴራል ደረጃ አካሂደናል። ይኽ መድረክ በየደረጃው የተሰበሰቡ የንግዱ ዘርፍ ጉዳዮች እና ሃሳቦች በሀገር አቀፍ እቅዶች እና የልማት ግቦች ዝግጅት ግብዓት ይሆኑ ዘንድ ለማካተት የተዘጋጀም ነው።

Read More

አሜሪካ እና ቻይና የንግድ ውጥረታቸውን ለማርገብ በለንደን እየመከሩ ነው

የአሜሪካ እና የቻይና ከፍተኛ ባለስልጣናት በሁለቱ ልዕለ-ኃያላን ሀገራት መካከል የተፈጠረውን የንግድ ውጥረት ለማርገብ ዛሬ በእንግሊዝ ለንደን ለውይይት ተቀምጠዋል። በዋሽንግተን እና በቤጂንግ መካከል ያለውን የንግድ ውጥረት ለማርገብ ባለፈው ወር በስዊዘርላንድ፣ ጄኔቫ ከተማ ሁለቱም ወገኖች አብዛኛውን ታሪፍ እንዲያነሱ ያስቻለ ቅድመ-ስምምነት ላይ ደርሰው ነበር። ዶናልድ ትራምፕ በአገራት ላይ ሊጥሉት ያቀዱትን ታሪፍ ለ90 ቀናት እንዲዘገይ ካሳወቁ በኋላ በአንጻሩ በቻይና…

Read More