“ኢትዮጵያ የአፍሪካ መቀመጫ የሆነችው በአጋጣሚ ሳይሆን ባላት ድንቅ ታሪክ ነው” – የሀገራት አምባሳደሮች
የብሔራዊ ቤተ መንግስት የኢትዮጵያ ታሪክ ከመጻኢ ጊዜዋ ጋር አስተሳስሮ የያዘ ድንቅ ስራ መሆኑን ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ገለጹ። የታደሰው ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ከትናንት በስቲያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በተገኙበት መመረቁ ይታወቃል። የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችም በብሔራዊ ቤተ መንግስት ጉብኝት አድርገዋል። በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ የኢትዮጵያ እና…
