በሚቀጥሉት 10 ቀናት በአብዛኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ ያመዝናል
በሚቀጥሉት 10 ቀናት በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የበጋው ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ የሚያመዝን መሆኑን የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሰሜን፣ ሰሜን ምሥራቅ፣ ምሥራቅ፣ መካከለኛው እና ደቡብ አከባቢዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ ቀጣይነት እንደሚኖረው ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡ በአጠቃላይ በሚቀጥሉት አስር ቀናት በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት ከኦሮሚያ ክልል ባሌ እና ምስራቅ ባሌ፣ ጉጂና ምዕራብ…
