Trendings

የተቀናጁ የምግብ ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋት እየተሰራ ነው

የተቀናጁ የምግብ ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋትና የምግብ ምርትን ለመጨመር እየተሰራ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ገለጹ። ከትናንት ጥቅምት 26 እስከ 28 ቀን 2017 ዓ.ም እየተካሄደ የሚገኘው “ከረሃብ ነፃ ዓለም” ዓለም አቀፍ ጉባዔ በዛሬው ዕለትም ቀጥሏል። በጉባዔው የዛሬ ውሎ ኢንቨስትመንትን ማስፋፋትና የድኅረ-ምርት ብክነት ላይ ያተኮሩ የፓናል ውይይቶች ተካሂደዋል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ጠንካራ…

Read More

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤቶችና መሰል ተቋማት ጉባዔ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሆና ተመረጠች

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤቶችና መሰል ተቋማት ጉባዔ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሆና መመረጧን የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ አስታወቀ። ከጥቅምት 20 እስከ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በዚምባብዌ ቪክቶሪያ ፎልስ ከተማ በተካሄደው 7ኛው የአፍሪካ ሕገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤቶችና መሰል ተቋማት ጉባዔ ላይ ነው ኢትዮጵያ የኮሚቴው አባል ሆና የተመረጠችው። ጉባኤው ”ሰብዓዊ ክብርን መሰረታዊ እሴትና መርህ ማድረግ…

Read More

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ለዶናልድ ትራምፕ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው በመመረጣቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷በቀጣይ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር በትብብር እንደሚሰሩ ገልጸዋል ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል

Read More

ሞትን አምልጠው፤ ምርጫን አሸንፈው ኋይትሃውስ የገቡት ፕሬዚዳንት

ዶናልድ ትራምፕ ሦስት ጊዜ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ለመሆን ሙከራ ከማድረጋቸው በፊት በአሜሪካ ታዋቂ እና አነጋጋሪ ቢሊየነር እንዲሁም በቴሌቭዥን መስኮት የማይጠፉ ዝነኛና አለፍ ሲሉም አስገራሚ ፖለቲከኛ ስለመሆናቸው ይነገራል። (Make American great again) አሜሪካንን መልሶ ታላቅ ማድረግ በሚለው መለያቸው በአውሮፓውያኑ 2016 ምርጫ ብቅ ያሉት ትራምፕ የሪፐብሊካን ፓርቲ ዕጩ ሆነው ነበረ ከዲሞክራቷ ሂላሪ ክሊንተን ጋር የተፎካከሩት። በ2016 የምርጫ ቅስቀሳቸው…

Read More

ሀገራዊ ሪፎርም ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት በእጥፍ አድጓል

ሀገራዊ ሪፎርም ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት በእጥፍ ማደጉን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ አስታወቁ፡፡ አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ማሻሻያ አዋጅ ከዚህ ቀደም ለረዥም ዓመታት ሲሠራበት የቆየውንና ለዋጋ ንረት ዋና መነሻ ነበር ሲባል በቆየው አሠራር ላይ ጠበቅ ያለ የማሻሻያ ድንጋጌ ይዞ መቅረቡን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ ከሴንትራል ባንኪንግ መጽሔት ጋር ባደረጉት…

Read More

የ’World Without Hunger’ ጉባኤ ተሳታፊዎችን እንኳን ወደ አፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና በሰለም መጣችሁ እላለሁ።

አለምአቀፍ መሪዎችን፣ ባለሞያዎችን እና የጉዳዩ ተቆርቋሪዎችን በአንድ ላይ በማምጣት እንዲወያዩ በማድረግ የጋራ ጥረቶቻችን ረሃብን በማጥፋት ለሁሉም የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ርብርብ ፍሬ እንዲያፈራ እንደሚያስችሉ ተስፋ አለኝ። በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ዓመታት በግብርና ሽግግር እና ምርታማነት ላይ በማተኮር የሠራነው ሥራ የታረሰ መሬታችን እጥፍ በማድረስ ከፍ ያለ እሴት ባላቸው የኢንደስትሪ አዝርዕት ምርት ላይ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች አስገኝቷል። በሚቀጥሉት ቀናት…

Read More

ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፈተ

ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፍቷል። ይህንን ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዱዓለም እና የመሀመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ዶክተር ከሊፋ ሙባረክ ከፍተውታል። በኮንፈረንሱ ላይ ከ16 ሀገራት የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የተቋማት መሪዎች እየተሳተፉ ነው። ኮንፈረንሱ በልዩ ልዩ መርሀ ግብሮች እስከ ነገ…

Read More

ዲጂታል ኢትዮጵያ ዕውን እንዲሆን የሳይበር ደህንነትን የማረጋገጥ ስራ በትኩረት እየተሰራ ነው -የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር

ዲጂታል ኢትዮጵያ ዕውን እንዲሆን የሳይበር ደህንነትን የማረጋገጥ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ትዕግስት ሀሚድ አስታወቁ። ለ5ተኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው አገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ዛሬ በድሬደዋ በፓናል ውይይት እየተከበረ ነው። በዚሁ ጊዜ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ትዕግስት ሀሚድ እንዳሉት በዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ውስጥ የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ…

Read More

በኮንፈረንስ ቱሪዝም በዓለም ላይ ስሟን የተከለችው አዲስ አበባ እንግዶቿን ተቀብላ ለማስተናገድ ተዘጋጅታለች – ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ

በኮንፈረንስ ቱሪዝም በዓለም ላይ ስሟን የተከለችው አዲስ አበባ እንግዶቿን በድምቀት ተቀብላ ለማስተናገድ ተዘጋጅታለች ሲሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ ገለፁ፡፡ ሚኒስትሯ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው፤ አዲስ አበባ በዚህ ወር ከምታስተናግዳቸው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች መካከል አንዱ የሆነው “ከርሃብ ነፃ አለም” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ጉባኤ ነገ እንደሚጀምር ገልፀዋል። በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ከጥቅምት 26 እስከ…

Read More

ኢትዮጵያና አልጄሪያ በወጣቶች የድንበር ተሻጋሪ በጎፈቃድ አገልግሎት በጋራ ለመስራት ተስማሙ

የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና ከአልጄሪያ አቻቸው ሙስተፍ ሂደዊ ጋር ተወያይተዋል። ፕሬዝዳንቶቹ ከአራተኛው የፓን አፍሪካ የወጣቶች ጉባኤ ጎን ለጎን ነው የሁለትዮሽ ውይይት ያካሄዱት። በውይይታቸውም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ በወጣት ፕሮግራሞች ልውውጥ በጋራ ለመስራት መምከራቸው ተገልጿል። ፕሬዝዳንቶቹ የወጣቶች የድንበር ተሻጋሪ በጎፈቃድ አገልግሎትን ለማስጀመር ከስምምነት መድረሳቸውም ተመላክቷል። ከስምምነት የደረሱባቸውን ጉዳዮች ወደ ስራ ለማስገባትና የመግባቢያ ስምምነት ለመፈራረም…

Read More