ኢትዮጵያ ዲጂታል ምጣኔ ሃብት ለመገንባት እያከናወነች ላለው ተግባር ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ቻይና አስታወቀች።
አሊባባ ግሎባል ኢኒሼቲቭ በኤሌክትሮኒክስ ንግድ ዙሪያ ከሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ጋር ውይይት እያደረገ ነው። በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ የምጣኔ ሀብትና ንግድ ጉዳይ ሚኒስትር ካውንስለር ያንግ ይሃንግ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ኢትዮጵያ ዲጂታል ምጣኔ ሀብትን ለመገንባት እያከናወነች ያለው ተግባር የሚበረታታ ነው። ለዚህም ቻይና ኤሌክትሮኒክ ንግድ (E-commerce)ን ጨምሮ ዲጅታል ኢኮኖሚን ለመገንባት በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ለሚገኙ ተግባራት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል አንስተዋል። የኢኖቬሽንና…
