Trendings

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የገለጻና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እያካሄደ ነው

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው የምክክር ምዕራፍ እንዲሁም ቀጣይ ውይይቶችን አስመልክቶ ለባለድርሻ አካለት ገለጻና የገንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እያካሄደ ነው። በመድረኩ የፓለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ ምሁራን፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ማኅበራት ተወካዮች፣ ከሦስቱ የመንግሥት አካላት የተወከሉ ተወካዮች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። ግንቦት 21 ቀን 2016 በአዲስ አበባ የተጀመረው የምክክር ምዕራፍ ከጠዋቱ መክፈቻ…

Read More

በቀጣዮቹ 10 ቀናት በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ስርጭት ይኖራል- ኢንስቲትዩቱ

በሚቀጥሉት አሥር ቀናት በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። በዚሁ መሰረት በሚቀጥሉት አሥር ቀናት ምሥራቅ እና ምዕራብ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ፣ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ ቡኖ በደሌ፣ ጅማ፣ ኢሉአባቦር፣ ማዕከላዊ እና ምዕራብ ጎንደር፣ አዊ ዞን፣ አሶሳ፣ ካማሺ፣ መተከል እና የማኦ ኮሞ ልዩ ዞን የተሻለ የዝናብ መጠን እንደሚኖራቸው የኢንስቲትዩቱ መረጃ አመላክቷል፡፡…

Read More

የፍትህ ዘርፍ ሪፎርም የመንግስት ዋነኛ የትኩረት አጀንዳ ነው ፦ አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

የፍትህ ዘርፍ ሪፎርም መንግስት ትኩረት የሰጠው ዋነኛ የትኩረት አጀንዳ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ። የሀገራዊ የፍርድ ቤቶችና የፍትህ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን የ2016 በጀት ዓመት የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ነው። የመድረኩ አላማ የአፈጻጸም ሂደቱን በመመልከት የመጡ ለውጦችን እና ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ያለመ መሆኑ ተገልጿል። አፈ ጉባኤ አቶ…

Read More

የህብረተሰብ ተወካዮች በአጀንዳ ሃሳቦች ላይ እያደረጉት ያለው ውይይት እንደቀጠለ ነው

ሁለተኛ ቀኑን ያስቆጠረውና የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ እያስተባበረ የሚኘው የምክክር ምዕራፍ ዛሬም ቀጥሏል፡፡ ከትናንት ግንቦት 21 ቀን 2016 ከሰዓት በኋላ ጀምሮ በነበረው መርሃ-ግብር ተሳታፊዎች በየህብረተሰብ ክፍላቸው በቡድን በመሆን ከወከሉት ማህበረሰብ በአደራ ያመጧቸው የአጀንዳ ሀሳቦች ላይ ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ በሂደቱ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የኛ የሚሉትን እና የተስማሙባቸውን የአጀንዳ ሀሳቦች በማጠናቀር ለኮሚሽኑ በቃለ-ጉባኤ ተፈራርመው…

Read More

የኮንስትራክሽን ዘርፉ በመሠረተ ልማትና በሥራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው – አቶ ተመስገን ጥሩነህ

ኢትዮጵያ ውስጥ የኮንስትራክሽን ዘርፉ በመሠረተ ልማትና በሥራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ቢግ 5 ኮንስትራክት ኢትዮጵያ 2024” የተሰኘ ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ አውደ ርዕይና ሲምፖዚየም በሚሊኒየም አዳራሽ ዛሬ መርቀው ከፍተዋል። “ኢትዮጵያን እንገንባ” በሚል መሪ ኃሳብ በሚካሄደው አውደ ርዕይ መክፈቻ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ…

Read More

ይህ የምክር ምዕራፍ በቀጣዩ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ምክክር የሚደረገባቸውን መሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ለመለየቱ ስራ ቁልፍ ሚና አለው – መስፍን አርዓያ(ፕ/ር)

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የከተማ አስተዳደርና ክልላዊ የምክክር ምዕራፍ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሯል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ÷ ኮሚሽኑ በምሁራን ፣ልሂቃንና በተለያዩ የፖለቲካ ተቋማት ጥያቄ የመንግስት ፈቃድና ፍላጎት ታክሎበት በ11 ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች በሚገባ ተቃኝቶ መቋቋሙን አውስተዋል፡፡ የተደራጁ የሃይማኖት፣ የሲቪል ማህበረሰብ እና የፖለቲካ ተቋምትን በየደረጃው በማካተት በ4 ምዕራፍ በከፋፈላቸው…

Read More

የኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ አመራሮች ካውንስል ተመሠረተ

በዚሁ ወቅት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እንደተናገሩት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለሀገራዊ ልማት በመካከለኛና ዝቅተኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሃይል በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። ተቋማቱ የክህሎትና የዕውቀት ሽግግር በማድረግ ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ተመሳሳይ ተልዕኮ ካላቸው ተቀማት ጋር ያላቸውን ግንኙነት በተደራጀ መልኩ ለማሳለጥ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ዘርፉን…

Read More

የህዝቦችን ተጠቃሚነትና የተመጣጠነ እድገት ለማረጋገጥ ገቢ የማመንጨት አቅምን ማጠናከር ይገባል፡- አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

የህዝቦችን ተጠቃሚነትና የተመጣጠነ እድገት ለማረጋገጥ ገቢ የማመንጨት አቅምን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያዘጋጀው የጋራ ገቢዎች አስተዳደርና ክፍፍልን በተመለከተ የፌዴራልና የክልል ባለድርሻ አካላት የጋራ ምክክር መድረክ በሀዋሳ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የተገኙት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር እንደገለጹት፤ የሀገሪቱ የጋራ ገቢዎች ቀመር ከ20…

Read More

በአዲስ አበባ አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ ዛሬ ይጀመራል

በአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ መርሃ ግብር የሚሳተፉ የህብረተሰብ ተወካዮች ወደ ተዘጋጀው ቦታ እየተሰባሰቡ ይገኛሉ። በአዲስ አበባ ከተማ በሚካሄደው የምክክር ምዕራፍ ከ2 ሺህ 500 በላይ ተወካዮች እንደሚሳተፉ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል፡፡ በምክክር ምዕራፍ መርሃ ግብሩ ሶስት ዋና ዋና ተግባራት የሚከናወኑ ሲሆን እነሱም ተሳታፊዎች በምክክርና በውይይት የአጀንዳ ሀሳቦችን ማምጣት፣ አጀንዳዎቻቸውን የጋራ በማድረግ ያሰባስባሉ፣ ያደራጃሉ እንዲሁም…

Read More

የምስራቅ አፍሪካ አገራት የባለብዙ ወገን ትብብራቸውን በማጠናከር ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት በጋራ ሊሰሩ ይገባል

የምስራቅ አፍሪካ አገራት የባለብዙ ወገን ትብብራቸውን በማጠናከር ለቀጣናው ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ተመራማሪዎች ገለጹ። በምስራቅ አፍሪካ የሚስተዋለው የኃይል ፉክክር በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር ፈተና እየሆነ መምጣቱንም አመላክተዋል። ምስራቅ አፍሪካ የአውሮፓ መካከለኛው ምስራቅና አፍሪካ የሚተሳሰሩበት ስትራቴጂካዊ ቀጣና ሲሆን፤ የዓለም ፖለቲካዊ ምጣኔ ኃብታዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴ መዘውር እንደሆነ ይታወቃል። ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምስራቅ ጋር…

Read More