ጠንካራ የፓርቲ አደረጃጀት በመትከል ተግባራትን በውጤታማነት መምራት ይገባል፦አቶ በላይ ተሰማ
በብልፅግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅ /ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ጋር በመሆን ያለፉትን ዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገምገማ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል። በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅ /ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ በላይ ተሰማ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት፥ ጠንካራ ፓርቲ የሚገነባው አባላት በጠንካራ አደረጃጀት ሲታቀፉ መሆኑን በመግለጽ፥ ጠንካራ የፓርቲ አደረጃጀት በመትከል ተግባራት በውጤታማነት…
