Trendings

የስራ እድል ፈጠራን በተመለከተ

በተያዘው በጀት ዓመት ለ4 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር እቅድ ተይዟል፡፡ከዚህም ውስጥ 700 ሺህ ለሚሆኑት የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ለመፍጠር እቅድ የተያዘ ሲሆን፤ ባለፉት ሶስት ወራት ለሰለጠኑ ለ100 ሺህ ዜጎች በውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ተፈጥሯል፡፡ ኮዲንግ እና የመረጃ ትንተናን ጨምሮ በርቀት ስራዎች ደግሞ ለ26 ሺህ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል፡፡

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የሰጡት ማብራሪያ፦ክፍል አንድ

ሀገራዊ ሪፎርምን በተመለከተበተለያዩ ዘርፎች ሲከናወኑ የነበሩ ሪፎርሞችን አጠናቀን ሀገራዊ ማንሰራራት የምንጀምርበት ዘመን የመጀመሪያ ምእራፍ ላይ ተገኝተናል፡፡ በመሆኑም በ2017 በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ የምናስመዘግብ ይሆናል፡፡ ከዚህ አኳያ ከትናንት እሳቤ ወጥተን በጋራ ወደ ነገ መሻገር አለብን፡፡ ኢኮኖሚያዊ እድገትን በተመለከተበ2016 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፡፡ ይህ በዓለም አቀፍ ደረጃም ትልቅ ስኬት ነው፡፡ በዘንድሮው በጀት…

Read More

የኑሮ ውድነትን በተመለከተ

የኑሮ ውድነትን በዘላቂነት መቅረፍ የምንችለው ምርታማነትን በመጨመር ነው፡፡ የንግድ ስርዓቱን ማዘምንም ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡ የኑሮ ውድነቱ እጅ አጠር ዜጎች ላይ ጫና እንዳይፈጥር መንግስት ከ300 እስከ 400 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት መድቧል፡፡ ማዕድ ማጋራት፣ ትምህርት ቤት ምገባ እና እሁድ ገበያ መንግስት አቅመ ደካሞችን ለማገዝ የሚያደርገው ጥረት አካል ነው፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም 249 ሺህ አቅመ ደካማ ዜጎች…

Read More

የመንግስት ገቢን በተመለከተ

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የመንግስት ገቢ በእጅጉን ጨምሯል፡፡ ባላፉት ሶስት ወራት 180 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጻር የተሻለ እድገት የተመዘገበበት ነው፡፡ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት የተሰበሰበው ገቢ 109 ቢሊዮን ብር ብቻ ነበር፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት አንጻር አሁንም ዝቅተኛ ገቢ የምትሰበስብ…

Read More

ኢትዮ-ቴሌኮም በኢትዮጵያ የዲጂታል ግብይት ሥርዓት እንዲጠናከር ገንቢ ሚና እየተጫወተ ነው

ኢትዮ-ቴሌኮም በኢትዮጵያ የዲጂታል ግብይት ሥርዓት እንዲጠናከር ገንቢ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባውን በመካሄድ ላይ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት በተነሱላቸው ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ እንዲሁም ቀጣናዊ፣ አሕጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ላይ…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፡-

👉 የዋጋ ግሽበት ባለፉት ዓመታት በርካታ ሀገራትን ፈትኗል ፤ ኢትዮጵያም የዋጋ ግሽበትን ለመቅረፍ በርካታ ስራዎችን እያከናወነች ነው፤ በተለይም ምርት ማምረት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ 👉 በሀገሪቱ የሚስተዋለውን የዋጋ ግሽበት ለመቅረፍም ከ300 እስከ 400 ቢሊየን ዶላር ለድጎማ ተይዟል፡፡ 👉 ባለፉት 3 ወራት ለነዳጅ ዘርፍ 35 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ተደጉሟል፤ በበጀት ዓመቱ ለሴፍቲነት 80 ቢሊየን ብር፣…

Read More

በተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ እየሰጡ የሚገኙት ኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢትዮጵያ የፋይናንስ ሴክተር ተጨባጭ እመርታ እያሳየ እንደሚገኝ የሚያመለክቱ የሚከተሉትን ተጨባጭ ማሳያዎች አንስተዋል፡-

በተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ እየሰጡ የሚገኙት ኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የኢትዮጵያ የፋይናንስ ሴክተር ተጨባጭ እመርታ እያሳየ እንደሚገኝ የሚያመለክቱ የሚከተሉትን ተጨባጭ ማሳያዎች አንስተዋል፡-

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፡-

👉 ባለፉት ሦስት ወራት 180 ቢሊየን ብር ገቢ ሰብስበናል፡፡ ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት 109 ቢሊየን ብር ነበር የተሰበሰበው፡፡ የልዩነቱ ስፋት ለውጥ እንዳለ እና መንገዳችን ትክክል እንደሆነ አመላክች ነው፡፡ 👉 በፌደራል መንግሥት 900 ቢሊየን ብር በክልሎች ደግሞ 600 ቢሊየን ብር ገቢ መሠብሰብ ከተቻለ በአጠቃላይ 1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ገደማ እንሰበስባለን ማት ነው፡፡ ይህም በቂ ባይሆንም ትልቅ…

Read More

ከኢንዱስትሪው ዘርፍ የ12.8 በመቶ ዕድገት ይጠበቃል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በተያዘው በጀት ዓመት ከኢንዱስትሪው ዘርፍ የ12.8 በመቶ ዕድገት እንደሚጠበቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፉት 3 ዓመታት በ”ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ የተሰሩ ሥራዎች ለዘርፉ መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል፡፡ ምርታማነትን ለማሳደግ በአምራች ዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ለመፍታት መንግሥት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በጨርቃ ጨርቅ፣ በምግብ እና መጠጥ፣ በኮንስትራክሽን፣ በኬሚካል እና በሌሎች…

Read More

የኢትዮጵያ አየር መንገድን በተመለከተ

በአፍሪካ ትልቁን የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እንቅስቃሴ ተጀምሯል፡፡ ይህ አዲስ የሚገነባው የአውሮፕላን ማረፊያም በዓመት ከ100 አስከ 130 ሚሊዮን መንገደኞችን ያስተነናግዳል፡፡ አሁን ላይ 124 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለማግዛት አዘናል፡፡ ይህም የኢትዮጵያ አየር መንገድን በአፍሪካ ትልቁ የአውሮፕላን ባለቤት ብቻ ሳይሆን ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ያለው ተቋም ያደርገዋል፡፡ ይህ ለውጥ በተለይ በአገልግሎት ዘርፍ ለማስመዝገብ የተያዘውን ውስጥ ለማሳካት ሚናው የጎላ ነው፡፡ በተያዘው…

Read More