Trendings

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ሴክቶሪያል ጉባዔ ተጠናቀቀ::

ቢሮው በሚዛን አማን ከተማ ሲያካሂድ የቆዬውን የ6 ወራት አፈፃፀምና የቀጣይ አቅጣጫዎች እንዲሁም ለተለያዩ የፋይናንስ ህግ ማዕቀፎች ዝግጅት ግብዓት ማሰባሰብ ላይ ያተኮረ ጉባዔ አጠናቋል። ጉባዔው በቆይታው የ2016 በጀት ዓመት የ6 ወራት የአፈፃፀም ሪፓርት በስፋት የተወያየበት ሲሆን በሪፖርቱ በተለይም ሲንከባለል የመጣ የግብዓትና የጡረታ ዕዳ ለማስመለስ የተከናወኑ ተግባራት አበረታች ቢሆኑም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተመላክቷል። የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት…

Read More

የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቦንጋ ከተማ ልዩ የ2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ መሠረተ ድንጋይ ለማስቀመጥ ቦንጋ ከተማ ገቡ::

የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቦንጋ ከተማ ልዩ የ2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ መሠረተ ድንጋይ ለማስቀመጥ ቦንጋ ከተማ ገብተዋል፡፡ ሚኒስትሩ ቦንጋ ከተማ ሲደርሱ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና ሌሎች የክልልና የካፋ ዞን ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ ደማቅ አቀባበል ተደርጎባቸዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በክልሉ በሚኖራቸው ቆይታ በቦንጋ…

Read More

በአገሪቱ የሚገኘውን የገጠር መሬት ምዝገባና ቅየሳ ሥራ አንድ ወጥ ሆኖ በክልሎች እንዲፈጸም የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ እንዲኖር በትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በረቂቅ አዋጅ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተደረገ ይገኛል። የኢፌዲሪ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 456/1997 ታውጆ ሥራ ላይ ከዋለበት ጊዜ ጀምሮ 19 ዓመታትን አስቆጠሯል። በመሆኑም አገሪቱ ከደረሰችበት የዕድገት ደረጃ እንዲሁም የአርሶና አርብቶ አደሩ ገቢ እያደገ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ በመሬት ላይ ያላቸው የመጠቀም መብትን ማሻሻያ እንዲደረግ አስገዳጅ ሁኔታ ተፈጥሯል ተብሏል። የገጠር…

Read More

የክልሉ ህዝብ የብዘሃ  ባህል ባለቤት መሆኑ አንዱ የቱሪዝም ፀጋ ነው።

ቱርዝም ለክልሉ ትልቅ የኢኮኖሚ አቅም በመሆኑ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቱሪዝም ፀጋዎች ዘርፈ ብዙ ናቸው። የክልሉ ህዝብ የብዘሃ  ባህል ባለቤት መሆኑ አንዱ የቱሪዝም ፀጋ ነው። ክልሉ የበርካታ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች መኖሪያ በመሆኑ ብዘሃ ባህል፣ ታሪክ፣ ቋንቋ፣ ቅርስ፣ የአኗኗር  ዘዬ እና የመሳሰሉት ህብረ-ብሔራዊ ውበትን የሚያጎሉና የቱሪዝም ሀብት የሚሆኑ ዕሴቶችና ትውፊቶች መናኸሪያ…

Read More

ክልላችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ምቹና በዘርፉ ለሚሰማራ አካላት ውጤታማ የሚያደረግ ነው-ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

በኢንዱስትሪ ሚኒስትር አዲሱ የአምራች ኢንዱስትሪ ፖሊሲና የተኪ ምርት ስትራቴጂ ላይ ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች የተዘጋጀ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በውይይት መድረኩ እንደገለጹት ክልላችን ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ምቹና በዘርፉ ለሚሰማራ አካላት ውጤታማነትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል። ክልሉ በአግሮ ኢንዱስትሪ፣…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ምክር ቤት ተቋቋመ

የተቋቋመው ምክር ቤት በክልሉ አደጋዎች እንዳይከሰቱ የቅድመ መከላከል እንዲሁም በተለያየ ምክንያቶች ለሚከሰቱ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ የመስጠት ተግባርን በበላይነት የሚመራ መሆኑ ተገልጿል። በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሰብሳቢነት የተቋቋመው ምክር ቤቱ ሌሎች የልማት ተቋማትንና የዞን አስተዳዳሪዎችን በውስጡ በአባልነት ያቀፈ ነው። የዞን መዋቅሮች በራስ አቅም የሚከሰቱ አደጋዎችን የመቋቋም አቋም መፈጠር እንዳለባቸው ያሳሰቡት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ምክር ቤት ተቋቋመ

የተቋቋመው ምክር ቤት በክልሉ አደጋዎች እንዳይከሰቱ የቅድመ መከላከል እንዲሁም በተለያየ ምክንያቶች ለሚከሰቱ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ የመስጠት ተግባርን በበላይነት የሚመራ መሆኑ ተገልጿል። በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሰብሳቢነት የተቋቋመው ምክር ቤቱ ሌሎች የልማት ተቋማትንና የዞን አስተዳዳሪዎችን በውስጡ በአባልነት ያቀፈ ነው። የዞን መዋቅሮች በራስ አቅም የሚከሰቱ አደጋዎችን የመቋቋም አቋም መፈጠር እንዳለባቸው ያሳሰቡት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት እና የካፋ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን በጋራ በሚሰሯቸው ጉዳዮች የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ::

የመግባቢያ ስምምነቱን የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ከካፋ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጋር ተፈራርመዋል ። በስምምነቱ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ስምምነቱ በክልሉ የሚከናወኑ የፖለቲካ፣የማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተግባራትን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል። የካፋ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን በክልሉ መኖሩ አንድ ለውጥ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠት ተደራሽነቱን ማጠናከር ይኖርበታል ብለዋል። ክልላዊ የሚዲያ…

Read More

በክልሉ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራጨ ያለዉን የወባ ወረርሽን ለመከላከል መንግስት በትኩረት እየሰራ ነዉ::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በሁለት ወቅታዊ ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለሚዲያ ተቋማት መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫው የክልላችን ህዝብ የጤና ስጋት የሆነው ወቅታዊ የወባ ወረርሽኝ ስርጭት እና ከጥር 23/2016 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ የሚከናወነው የተፋሰስ ንቅናቄ ላይ ያተኮረ ነው። መግለጫ የሰጡት የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ…

Read More