ብልጽግና ፓርቲ ያስጀመራቸውን የለውጥ ጉዞ በመደገፍ ሀገራችንን ወደ ሚገባት ከፍታ ማድረስ ያስፈልጋል ሲሉ ያነጋገርናቸው ተሳታፊዎች ገለጹ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ”ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ማኒፌስቶ እና ምርጫ ምልክት ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በቦንጋ ከተማ አካኺዷል። በመርሃ ግብሩ ወቅት ያነጋገርናቸው ተሳታፊዎች እንደገለጹት: ፓርቲው ሀገሪቱን ማስተዳደር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በወሰዳቸው እርምጃዎች ውስብስብ ችግሮችን መስመር እያስያዘ መሆኑን ተናግረዋል። ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ እርምጃዎቹ ተጠቃሚ ያልሆነ የሕብረተሰብ…
