Trendings

በካፋ ዞን የተለያዩ ከተማ አስተዳደሮች “የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመቅረፍ የኢትዮጵያን ማንሰራራይ እውን እናደርጋለን!” በሚል መሪ ሃሳብ ከነዋሪዎች ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው።

መድረኮቹ በሁሉም ዘርፎች የተመዘገበዉን ለዉጥ በማስቀጠል የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቅነት በመፍታት የህዝቡን ተጠቃሚነት በሁሉም ዘርፍ ማረጋገጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያጠነጠነ ነው። የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ውይይቱን የመሩት የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ መጠነ ሰፊ ተግባር መከናወኑን ገልጾ በዚህም ለህዝብ ድምፅ ትኩረት በመስጠት ማዘጋጃ ቤት ላይ ያደረገው የሪፎርም ስራና 13…

Read More

በኮንታ ዞን 18 አመራሮች ከኃላፊነት ተነሱ

በኮንታ ዞን አመራር ውጤታማነትን፣ ስነ ምግባርንና ዝግጁነትን መሠረት ባደረገ ጥብቅ ምዘና፣ በዞኑ የሚገኙ 71 አመራሮችን ከዞን እስከታችኛዉ መዋቅር የማንሳት፣ የማሸጋሸግና አዲስ ምደባ ማከናወኑን የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ ገዝሙ ተናግረዋል። በዚህም መሰረት፡ 18 አመራሮች ከኃላፊነት ተነስተዋል። 25 አመራሮች ሽግሽግ ተደርጓል። 28 አዳዲስ አመራሮች ወደ ኃላፊነት መጥተዋል። ይህ እርምጃ በተለይ ወጣቶችንና ሴቶችን ያገናዘበ መሆኑ…

Read More

በክልሉ የአርሶ አደሮች መስክ ትምህርት ቤት የግብርና ቴክኖሎጂ ሥርፀት ማዕከል እንዲሆን ሥራዎች እየተከናወነ ይገኛል፦አቶ ማስረሻ በላቸው

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ SNV HORT LIFE 3 ፕሮግራም ጋር በመተባበር የአርሶ አደር የመስክ ትምህርት ቤት ተቋማዊ ማድረጊያ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ነው። በመድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በክልሉ (SNV HORT LIFE 3) ፕሮጀክት በ18 ወረዳዎች የሚሰራ ሲሆን ከዚህም በ11 ወረዳዎች በቀጥታ እና በቀሪ…

Read More

በዳውሮ ዞን 59 አመራሮች ከኃላፊነታቸው ተነሱ

በዳውሮ ዞን በቅርቡ በተደረገ ጥብቅ ግምገማ ላይ ተመስርቶ በተወሰደው እርምጃ ከዞን አስከታችኛዉ መዋቅር 59 አመራሮች ሙሉ በሙሉ ከኃላፊነታቸው የተነሱ ሲሆን፣ ሌሎች 55 አመራሮች ደግሞ የኃላፊነት ሽግሽግ ተደርጓል። የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ኢዮብ ቶማስ እንደገለጹት፣ ይህ እርምጃ የተወሰደው ያለፈውን ዓመት አፈጻጸም ከመዘነ በኋላ መጪውን ተልዕኮ በብቃትና በስነ ምግባር ሊያስፈጽም የሚችል ጠንካራ…

Read More

የኢትዮጵያ የሚዲያ ልህቀት ማዕከል ስራ ጀመረ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የመገናኛ ብዙሃንን አቅም ለማሳደግ በሚል ያቋቋመው የሚዲያ ልህቀት ማዕከል በይፋ ስራ ጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እንዳሉት፤ በሰላም፣ በመልካም አስተዳደር ዘርፍም ሆነ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ወቅታዊና ትክክኛ መረጃ በማቅረብ መገናኛ ብዙሃን ሚናቸው የጎላ ነው። ሚዲያዎች ለማህበረሰብ እድገት የራሳቸውን ሚና በመጫወት የኢትዮጵያን እድገት ለማረጋገጥ…

Read More

የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ቀዳሚ ትኩረት መሆኑ ተገለጸ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል፣ የህዝብን ተጠቃሚነት ማረጋገጥን ማዕከል ያደረገ የክልልና የዞን ምክር ቤቶች የ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ግምገማ በታርጫ ከተማ ተጀመረ። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ፣ የምክር ቤት አባላት በየደረጃው የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከምንጊዜውም በላይ በትጋት እንዲሰሩ አሳስበዋል። “በሩብ ዓመቱ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠልና የታዩ…

Read More

የሕብረተሰብ ተሳትፎን ሁሉም ተቋማት ባህል አድርጎ በመስራት ውጤት ማስመዝገብ ይገባቸዋል። አቶ ፋጂዮ ሳፒ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት የ2018 ዓ/ም የመሠረተ ልማት ክላስተር ተቋማት የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም እና የቀጣይ አቅጣጫዎች የተግባቦት መድረክ በሚዛን አማን ከተማ ተካሂዷል ። በዚህም የክላስተር ተቋሟት የሆኑት የክልሉ ትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ፣ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፣ የውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ እና አርብቶ አደርና ቆላማ አካባቢ ጉዳይ ቢሮዎች የ1ኛ ሩብ ዓመት ሪፖርታቸውን…

Read More

የመደመር መንግሥት

የመደመር መንግስት የነገን የተሻለ ለማድረግ የትናንት፣ የዛሬን የነገ ተደራራቢ ኃላፊነቶቻችንን በአስቸኳይ እንድንወጣ ያደርጋል። እንዲሁም ተለዋዋጭ በሆነዉ የዓለም ሁኔታ ውስጥ፣ ጥንካሬያችንን ለማረጋገጥና ከግባችን ለመድረስ እንድንፈጥን ያስችላል። የመደመር መንግስት ፍጥነትና መስረት ያደረገ ዕሳቤ ነዉ። የዚህ መጽሐፍም ዋነኛ ጭብጥ ይህንን የፍጥነትና የፈጠራ ፍኖት ማብራራት ነዉ። ሀገራችን ካለችበት የግርጌ ደረጃ ተሰፈንጥራ ወደ ራስጌ መዉጣት የምትችልበትን ሐሳብ የሚያቀብል ነዉ። በዋናነት…

Read More

አየር ኃይል የትኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል – ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ

አየር ኃይል የሚሰጠውን ማንኛውንም ግዳጅ ለመፈፀም በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል አሉ የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ፡፡ የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ለአየር ኦፕሬሽን በግዳጅ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ክፍሎች እውቅና ሰጥቷል፡፡ ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ በዚህ ወቅት÷ተቋሙ የሚሰጠውን ተልዕኮ እና ግዳጅ ለመፈፀም በከፍተኛ የዝግጁነት አቅም ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል ። አየር ኃይል በአጭር ጊዜ…

Read More

ከህዝብና ከመንግሥት የተሰጠውን ተልዕኮ መወጣት የሚያስችል የፖሊስ ቁመናን በመገንባት የህግ በላይነትን ማረጋገጥና ዘላቂ ሠላምን ማስፈን ይገባል ፦ አቶ አንድነት አሸናፊ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረክ በቦንጋ እያካሄደ ነው። በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ ባለፉት ዓመታት በዘርፉ በየደረጃው ካሉት የባለድርሻ አካላት ጋር በተሰራው ስራ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል ። በዚሁም በየአካባቢው ፖሊስ የተሟላ ቁመና በመያዝ የወንጀል…

Read More