የጠ/ሚ ናሬንድራ ሞዲ ጉብኝት ኢትዮጵያ በባለብዙ ዋልታ ዓለም ግንባታ ላይ ያላትን ቁልፍ ሚና ያረጋገጠ ነው – የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት ኢትዮጵያ የባለብዙ ዋልታ ዓለም ግንባታ ውስጥ ያላትን ቁልፍ ሚና ያረጋገጠ ነው አለ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት። አገልግሎቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በኢትዮጵያ እያደረጉት ያለውን ጉብኝት አስመልክቶ ያስተላለፈው መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦ የኢትዮጵያና ሕንድ የስትራቴጂካዊ አጋርነት አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ! ይህ ጉብኝት በብሔራዊ ቤተመንግሥት ከተደረገው ደማቅ አቀባበል ባለፈ፣ ኢትዮጵያ በዓለም…
