በዞኑ ታሪካዊ ዋሻዎችንና የተፈጥሮ መስህቦችን በማልማት ለወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ሸካ ዞን ገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የምትገኘውና በአብዛኛው ጥቅጥቅ ባሉ ደኖች የተሸፈነችው ሸካ ዞን፣ በውስጧ ያቀፈቻቸውን ታሪካዊና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መዳረሻዎችን የመለየትና የማልማት ስራ መጀመሩን የዞኑ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው የቱሪዝም ፕሮሞሽንና ግብይት ቡድን መሪ አቶ ብርሃኑ አያሾ እንደገለጹት፣ በዞኑ ወረዳዎችና ከተሞች በጥናት ላይ የተመሰረተ የመስህብ ስፍራዎችን የመለየት ስራ ተከናውኗል። ይህ ጥረትም ዞኑ ከያዘው የተፈጥሮ…
