“ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት ለዚህ ፓርላማ፣ ለሕዝባችሁ እና ለዴሞክራሲያዊ ጉዟችሁ ታላቅ አክብሮት በመስጠት ነው” – ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ
ለሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ ላይ ንግግር አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግራቸውን የጀመሩት “ዛሬ እዚህ ፊታችሁ ስቆም በታላቅ ክብር ነው፤ “የአንበሶቹ ምድር በሆነችው በታላቋ ኢትዮጵያ መገኘት እጅግ ታላቅ የደስታ ስሜት የሚሰጥ ነው፤ እኔ የተወለድሁባት የሕንዷ ጉጅራትም የአንበሶች ቤት ናት፤…
