በመንግስት ላይ 52 ሚሊየን ብር ኪሳራ አድርሰዋል የተባሉ ግለሰቦች በከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰሱ
የቀድሞ የፕራይቬታይዜሽን እና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በመንግስት ላይ 52 ሚሊየን ብር ኪሳራ አድርሰዋል የተባሉ ሦስት ግለሰቦች በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡ ተከሳሾቹ በመንግስት ይዞታ ስር ሲተዳደር የነበረው አደይ አበባ ድርና ማግ ፋብሪካ ተገቢ ባልሆነ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ልብስ ስፌትና ጨርቃ ጨርቅ አ.ማ እንዲቀየር አድርገዋል በሚል ነው ክስ የተመሰረተባቸው። 1ኛ…
