የክልሉ ግቢርና ቢሮ ሆርቲ ካልቸር ልማት በአቮካዶ ማጋባት/ Grafting/ ዙሪያ ለዞንና ለወረዳ ግብርና ባለሙያዎች ስሰጥ የነበረዉ ስልጠና ተጠናቀቀ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ በእርሻና ሆርቲ ካልቸር ልማት በአቮካዶ ማጋባት/ Grafting/ ዙሪያ ለዞንና ወረዳ ግብርና ባለሙያዎችና ለችግኝ ጣቢያ አስተባባሪዎች በቴፒ ከተማ ለተከታታይ ሶስት ቀናት ስሰጥ የነበረዉ የአሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቋል። ስልጠናዉ በአቮካዶ ማጋባት/ Grafting/፣ የፓፓያ ተክል አመራረትና በሆርቲካልቸር ሰብል ላይ የሚከሰቱ ተባዮች ዙሪያ ሰነድ ቀርቦ ገለፃ የተደረገበት ስሆን በዛሬዉ ዕለት በቴፒ ግብርና ምርምር…
