Trendings

በመንግስት እየተመቻቸ የሚገኘዉን የዉጭ ሀገር የስራ ስምሪት እድል ህብረተሰቡ በአግባቡ ሊጠቀም እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ጥሪ አቀረበ።

ይህም በህገ-ወጥ መንገድ ለስራ ፍለጋ ከሀገር የሚወጡ ዜጎች ላይ የሚደርሰዉን በደሎችና የመብት ጠሰቶችን ጥሰቶች የሚስያቀር መሆኑም ተጠቁሟል። የዉጭ ሀገር የስራ ስምሪት መንግስት ሰራተኛ ከሚፈልጉ ሀገራት ጋር ህጋዊ ስምምነት በመፈፀም ክህሎት ያላቸዉ ዜጎች ደንነታቸዉ ተጠብቆ ወደ ዉጭ ሀገር በመሄድ የስራ ዕድል የሚጠቀሙበት አሰራር መሆኑን የቢሮዉ ምክትል ሀላፊና የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሀላፊ ዶክተር ተክለአብ ቡሎ ተናግረዋል። ይህም…

Read More

ቆይታ ከእኛ ጋር

የትራንስፖርት አገልግሎት ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና አስተዳደራዊ ጉዳዮች እንዲሳለጡ ከፍተኛ ሚና ከሚጫወቱ ዘርፎች አንዱና ዋነኛው መሆኑን በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ማረጋገጥ እንችላለን። የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ዘርፍ በአስፈላጊነቱ ልክ በተዋንያኖቹ ምክንያት በሚፈጠሩ ህገ ወጥ አሰራሮች በዜጎች ላይ የኑሮ ጫና ከመፍጠሩም በላይ ለመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችም ሰፊውን ድርሻ እንደሚወስድ አጠያያቂ አይደለም።ከቅርብ ጊዜ ወድህ በዓለም አቀፍ ገበያ ጫና የነዳጅ እና መለዋወጫ እቃዎች ዋጋ…

Read More

በክልሉ በሚከናወነው የልማት ሥራዎች የላቀ የኅብረተሰብ ተሳትፎ እየተመዘገበ ነው ፦ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

እየተካሄደ በሚገኘው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ፣ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ምላሽ ሰጥተዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት÷ በክልሉ የኅብረተሰብ የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ሰፊ ትኩረት ተሰጥተው እየተሰራ መኾኑን በማንሳት በዚህም ከጊዜ ወደ ጊዜ የኅብረተሰብ እርካታ…

Read More

በቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ በአቶ ጌዲዮን ኮስታብ የተመራ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎችና የአመራር ቡድን በጉራፈርዳ ወረዳ በርጂ ቀበሌ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎበኙ።

በቀበሌዋ የታዩ የልማት ስራዎችና የተቋማት የግንባታ ሂደቶች ለሌሎች መዋቅሮች ተሞክሮ የሚቀመርበት ነው ብለዋል። በቤንች ሸኮ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ በአቶ ጌዲዮን ኮስታብ የተመራ የዞን ፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋናና ምክትል አፈ ጉባኤዎች ፣ የቋሚ ኮሚቴ አባላት በወረዳው በርጂ ቀበሌ በመገኘት የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ በቀበሌው የምክር ቤት አባል በሆኑት በአርሶ አደር…

Read More

የክልሉ አስፈፃሚ ተቋማት የዕቅድ አፈጻጸም እየተገመገመ ይገኛል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአስፈጻሚ ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የተግባር አፈጻጸም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በተገኙበት በቦንጋ ከተማ እየተገመገመ ነዉ። በበጀት ዓመቱ ታቅዶ ወደ ተግባር በተገቡና ባለፉት ስድስት ወራት የተከናወኑ አንኳር ተግባራት አፈጻጸም በዝርዝር እየቀረበ ይገኛል። የክልሉን ህዝቦች የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታትና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሰሩ ዋና ተግባራት…

Read More

ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን “ህፃናት የሚሉት አላቸው እናዳምጣቸው! ” በሚል መሪ ቃል እንደሚከበር ተገለጸ

የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን ለማክበር ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገልጿል ፡፡ የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ገነት መኩሪያ እንደገለጹት ዓለም አቀፍ የህፃናት ቀን የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ አካል የሆነው የአለም ህጻናት መብቶች ኮንቬንሽን እ.ኤ.አ ኑቬምበር 20/1989 ዓ.ም በተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባዔ ፀድቆ በስራ ላይ እንዲውል…

Read More

ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የሀገሪቱን  ምርት (GDP) እስከ 12 በመቶ እንዲያግዝ እየተሰራ ነው:- የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ

#ሪፖርታዥ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የሀገሪቱን  ምርት (GDP) እስከ 12 በመቶ እንዲያግዝ እየተሰራ ነው:- የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ ሀገራችን ኢትዮጵያ ዲጂታል ፖሊሲ አርቅቃ ሲትተገብር ቆይታለች፤ ከእነዚህም አንዱ ላለፉት 5 ዓመታት  ሲሰራበት  ቆይተው ታህሳስ 2018/2028  የተጠናቀቀው  ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ነው። በእነዚህ ማዕቀፎች ሲሰሩባቸው ከቆዩት ጉዳዮች ዲጅታል ግብይት፣ ዲጂታል ልማቶች፣ ቴክኖሎጂ መር የመንግስት አገልግሎቶችን በተደራጀ መንገድ ማስከድና መሠረተ ልማቶችን…

Read More

6 ሺህ ሕብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የቻይት ንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በምዕራብ ኦሞ ዞን ማጂ ወረዳ የተገነባው የቻይት ንጹህ መጠጥ ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ። የቻይት ንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ ሲሆን 6ሺህ የአከባቢ ሕብረተሰብ ክፍሎችንም ተጠቃሚ ያደርጋል። በምረቃዉ ወቅት የክልሉ ውሃ ማዕድና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር…

Read More

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በአረንጓዴ የልማት ጉዞ በርካታ ተግባራትን በቁርጠኝነት በማከናወን ላይ ትገኛለች-ሳሙኤል ዶ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በአረንጓዴ የልማት ጉዞ በርካታ ተግባራትን በቁርጠኝነት በማከናወን ላይ እንደምትገኝ የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ሳሙኤል ዶ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ ሳሙኤል ዶ (ዶ/ር) እንዳሉት ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት አመታት በአረንጓዴ ልማት ያስመዘገበችው ውጤት አስደናቂ እና ለሌሎች ምሳሌ ሊሆን የሚችል ነው፡፡ “ኢትዮጵያ አረንጓዴ ጉዞ 2030” በሚል መሪ ሃሳብ አመታዊ የልማት ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ…

Read More