Trendings

Getenesh Gebeyehu

የሀገር አቀፍ እና የፌዴራል ባለድርሻ አካላት እነማን ናቸው ?

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገር አቀፍ እና የፌዴራል ባለድርሻ አካላት በአጀንዳ ማሰባሰብ የሚሳተፉበትን መድረክ ለማዘጋጀት እየተሰናዳ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ኮሚሽኑም በሀገር አቀፍ እና በፌዴራል ደረጃ በምክክር ሂደቶች እንዲሳተፉ ከለያቸው ባለድርሻ አካላት አጀንዳ ለማሰባሰብ ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም አሳውቋል፡፡ በዚህ ሂደት ኮሚሽኑ በሀገር አቀፍ እና በፌዴራል ደረጃ ለሚገኙ የሃይማኖት ተቋማት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ ማህበራት፣ የፖለቲካ…

Read More

የብራዚል አውሮፕላን አምራች ኩባንያ በኢትዮጵያ መሥራት እንደሚፈልግ ገለፀ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዶ/ር ዓለሙ ስሜ የብራዚል ምክትል አምባሳደር ጃክሰን ሊማን ጨምሮ ኢምብሬር የተባለው የሀገሪቱ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ የስራ ኃላፊዎችን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። መንግሥት ለአቪዬሽን ዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ሚኒስትሩ በውይይቱ ላይ አንስተዋል። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከዓለም ጋር በማገናኘት የአህጉሪቱ ኩራት ሆኖ እንዲዘልቅ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። በአቪዬሽን ዘርፍ የተሰማሩ…

Read More

በኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ የተራቆቱ ቦታዎች ወደነበሩበት እንዲመለሱ እየተሠራ ነው

በኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ የተራቆቱ ቦታዎችን ቀድሞ ወደነበሩበት ተፈጥሯዊ ይዞታ የመመለስ ሥራ እየተከናወነ መሆኑ ተገለፀ፡፡ በፕሮጀክቱ የአካባቢያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ዕቅድ ሥራ አስኪያጅ ግዛቸው ደሳለኝ እንደገለፁት፤ ለፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ግብዓት የተቆፈሩ እና ተረፈ ምርቶች ተጠራቅመውባቸው የነበሩ ቦታዎችን ወደ ተፈጥሯዊ ይዞታቸው የመመለስ ሥራ እየተሠራ ነው፡፡ በዚህም ፕሮጀክቱ ራሱን የቻለ የሥራ ቡድን እና የችግኝ ጣቢያ…

Read More

ክልሉ ከ41 ሺህ ቶን በላይ የቅመማቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ

በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ41 ሺህ ቶን በላይ የቅመማቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ቡና፣ ሻይ እና ቅመማቅመም ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ በክልሉ ከ90 ሺህ ሔክታር በሚልቅ መሬት ላይ የቅመማቅመም ምርት እየለማ መሆኑን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አሥራት መኩሪያ ተናግረዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ከ56 ሺህ ቶን በላይ ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን አውስተው፤ ባለፉት…

Read More

በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በዋና ዋና ዘርፎች አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል። ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ2017 በጀት ዓመት የ9 ወራት ክልላዊ የመንግሥት እና የፓርቲ ተግባር አፈጻጸም በቦንጋ ከተማ እየተገመገመ ይገኛል። በግምገማ መድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፥ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በዋና ዋና ዘርፎች አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል። በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የተለያዩ የግብርና ቴክኖሎጂዎች በማስፋትና የግብዓት አጠቃቀም በማሻሻል…

Read More

በምዕራብ ኦሞ ዞን ሱሪ ወረዳ በተከሰተው የአባ ሳንጋ በሽታ ህብረተሰቡ ላልተወሰነ ጊዜ በዞኑ ውስጥ ጥሬ ስጋ መመገብ እንደማይገባቸው የዞኑ ጤና መምሪያ አስታወቀ

በምዕራብ ኦሞ ዞን በሱሪ ወረዳ በኮካ ቀበሌ የተከሰተው የአባ ሳንጋ በሽታ የመከላከል ሥራዎች ላይ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ። የዞኑ ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሼማጂ ጉሪጭማ እንደተናገሩት በዞኑ በሱሪ ወረዳ በአባ ሳንጋ በሽታ የሞተ ሰው አለመኖሩን ያስታወቁት ኃላፊው በዞኑ አርብቶ አደር መምሪያ ኃላፊ አማካይነት ሰባት ሰዎች በአባ ሰንጋ በሽታ ሞቱ ተብሎ ለDW የተሰጠዉ መረጃ ስህተት፣ ያልተገመገመና በዞኑ…

Read More

#ሪፖርታዥ

የመማር ማስተማር ሥራን ውጤታማ ሊያደርጉ የሚችሉ  ትምህርታዊ ኢንሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየሆኑ ነዉ ፦የክልሉ ትምህርት ቢሮ በክልሉ የመማር ማስተማር ሥራን ውጤታማ ሊያደርጉ የሚችሉ የተለያዩ ትምህርታዊ ኢንሼቲቮች ተቀርጸዉ እየተተገበሩ እንደሚገኙ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት ትምህርት ቢሮ ገለጸ። የመማር ማስተማር ሥራን ውጤታማ ለማድረግ ተቀርጸዉ እየተተገበሩ ከሚገኙ ሂደታዊ ከሆኑ ከተለያዩ ኢንሼቲቮች ወይም ትምህርታዊ ፕሮግራሞች አንዱ የትምህርት ቤት…

Read More

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ36 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ከክልሉ ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ36 ሺህ 600 ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ቡና፣ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን አስታወቀ። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ አሥራት መኩሪያ፥ በክልሉ የቡናን ምርታማነት ለማሳደግ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግና የግብይት አቅርቦት ሥራን በማዘመን ውጤታማ ሥራ መከናወኑን ለኢዜአ ተናግረዋል። በክልሉ በቡና ማሳ ከተሸፈነው ከ582…

Read More

ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና የማዕከላዊ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ዘውዱ በላይ በምዕራብ ኦሞ ዞን እየተሠሩ ያሉ የፀጥታ ሥራዎችን ገመገሙ

ከዞኑ ከተለያዩ ወረዳዎች ከተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በተደረገው ውይይት መድረክ እስካሁን በዞኑ ከፌደራል ጀምሮ የነበረው የፀጥታ አካላትና አመራሩ ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት በተሠራው ሥራ የተሻለ ሠላም በአከባቢው እየመጣ መሆኑን ተሳታፊዎች አንስተው የተጀመረው ሥራ ተጠናክረው እንድቀጥልና ዘላቂነት ሠላም ማረጋገጥ እንድሠራ አሳስበዋል:: ከዚህም ባሻገር በአከባቢው ለፀጥታ ስጋት የሚሆኑ ጉዳዮችን ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት መፍታትና የመከላከያ ሠራዊት ድንበር አከባቢ ጥበቃ…

Read More

በፓርቲያችን መሪነት ጠንካራ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል ፦አቶ ነጋ አበራ

በፓርቲያችን ብልጽግና መሪነት የተደራጀ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር ውጤታማ ስራዎች መመዝገቡን የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ ገለጹ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ይገኛል፡፡ በመድረኩ መክፈቻ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት…

Read More