በዞኑ በገጠርና በከተማ ለኢንቨስትመንት ከተላለፈው 47ሺ 853 ሄክታር መሬት ውስጥ የለማው ከ28 ሺ ሄር በላይ እንደማይበልጥ የቤንች ሸኮ ዞን ንግድ እና ኢንበስትመንት መምሪያ አስታወቀ ።
የቤንች ሸኮ ዞን ዞናዊ የኢንቨስትመንት ፎረም መድረክ በሚዛን አማን ከተማ መካሄድ ጀምሯል። “ኢንቨስትመንት ለሁለንተናዊ ብልጽግና “በሚል መሪ ቃል የቤንች ሸኮ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ በዞኑ ካሉ ባለሀብቶች ፣ አመራሮች እና አጋር አካላት ጋር የኢንቨስትመንት ፎረም መድረክ እያካሄደ ነው። የዞኑ ዋና አስተዳደሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት በዞኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ የኢንቨስትመንት ፍሰቱ እያደገ እንደሆነ…
