ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከቻይና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከቻይና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ሹዌ ቢንግ ጋር በጽ/ቤታቸው ተወያይተዋል። ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነት በሁኔታዎች የማይቀያየር ስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ ላይ መድረሱን በመግለጽ፤ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ለምታደርገው ጥረት የቻይናን ድጋፍ ጠይቀዋል። ኢትዮጵያ በቻይና-አፍሪካ ትብብር ፎረም (FOCAC) የተቀመጡ ግቦችን ከአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ…
