ተማሪዎች ከቀለም ትምህርት ጎን ለጎን በሙያዊ ዕውቀት እንዲጎለብቱ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ትምህርት ቢሮ የ2017 ዓ.ም የስራ እና ቴክኒክ ትምህርት በኮንታ ዞን ጪዳ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አስጀመሯል። በክልሉ በ2017 ትምህርት ዘመን ከ16 ሺህ በላይ ተማሪዎች በሙያ ለመማር መመዝገባቸው ታውቋል። በማስጀመሪያ መርሀ-ግብር ላይ የተገኙት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊና የስርዓተ-ትምህርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አባቴ ኡቃ በሀገራችን ያለውን የትምህርት ስብራት ለመጠገን በተጠናው አዲሱ ፍኖተ…
