“የህልም ጉልበት ለእመርታዊ እድገት በሚል መሪ ሀሳብ መነሻ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በየደረጃው ለሚገኙ ለክልላችን ብልጽግና ፓርቲ አመራር አካላት ሲሰጥ የነበረው የመጀመሪያ ዙር ስልጠና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
የዚህ ስልጠና ዋናው አላማ አርቆ በማሰብና አልቆ በመስራት በሁሉም መስክ እመርታን ማስመዝገብ እንዲቻል አመራሩን በፓርቲያችን ህልምና ትልም ዙሪያ መግባባትን መፍጠር፤ የመፈፀም ብቃቱ የጎለበተ አመራር ለመፍጠር አቅም መገንባትና የአስተሳሰብና ተግባር አንድነትን ለማምጣት ታስቦ የተሰጠው ስልጠና በጥሩ መንፈስ ተጠናቋል። ከዚህ ስልጠና በኋላ አመራሩ ቁጭትና መነሳሳትን በመፍጠር አቅሞችን ወደ ውጤት ለመቀየር፣ በየደረጃው ለሚነሱ ጥያቄዎች ተግባራዊ ምላሽ ለመስጠትና ማህበረሰባዊ…
