በ11 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባ የቦባ ቆጫ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታው ተጠናቅቆ ተመረቀ።
ትምህርቤቱ በኢፌዴሪ ገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉሙሩክ ኮሚሽን በጋራ መገንባቱ ተገልጿል ። በክልሉ ካፋ ዞን ዋቻ ከተማ የተገነባው የቦባ ቆጫ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾና የገቢዎች ሚኒስትር ዴኤታና የጉምሩክ ኮሚሽን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተመርቋል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ባስተላለፉት መልዕክትም የትምህርት ተቋማት መሠረታዊ ችግሮች መጠነ ሰፊ በመሆናቸው ችግሮችን ለመፍታት ደረጃ…
