Trendings

Getenesh Gebeyehu

አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት የሆነች ሀገር የመገንባት ራዕይን ከግብ ለማድረስ ሁለንተናዊ የልማት ዕቅዶቻችን ሳይቆራረጡ ተግባራዊ ማድረግ ይገባል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ፡፡

የፌደራል ተቋማት የሱፐርቪዥን ማጠቃለያ ሪፖርት ግምገማ ዛሬ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ ከመስክ ምልከታ የተገኙ ሪፖርቶችን ጨምሮ የተቋማት አፈፃፀም ጠለቅ ባለ እና በተደራጀ መልኩ ሪፖርት ቀርቧል፡፡ ዕቅዶች መሬት ላይ ወርደው ሲተገበሩ ምን ውጤት አመጡ፣ በትግበራ ሂደቱ ያጋጠሙ ችግሮች ምን ይመስላሉ፣ እንዲሁም በቀጣይ በመረጃ እና በትንተና የተደገፈ አካሄድ እንዴት መፍጠር እንደሚቻል በመድረኩ ተነስቷል፡፡ በሱፐርቪዥኑ ሪፖርት በመልካም ጅማሮ የታየው ዋንኛው…

Read More

ወደ ማህበረሰቡ ለሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የጤና አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

የጤና ሚኒስቴርና የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ወደ ማህበረሰቡ ለሚቀላቀሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የጤና አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ። መንግስት የቀድሞ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉና ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ በብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽኑ እየሰራ ይገኛል፡፡ በተለይም የቀድሞ ታጣቂዎች ትጥቅ ከማስፈታት ጀምሮ መልሶ የማቋቋም ስራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ይገኛል። የቀድሞ ታጣቂዎችን ለሰላምና ምርታማነት ለማዘጋጀትም ማህበራዊ…

Read More

ብልፅግና ከፖለቲካ ፓርቲዎችና ከሲቪክ ማህበራት ጋር ከመቼውም በላይ ተቀራርቦ እየሰራ ነው – አቶ መለሰ ዓለሙ::

ብልፅግና ፓርቲ ከፖለቲካ ፓርቲዎችና ከሲቪክ ማህበራት ጋር ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቀራርቦ እየሰራ መሆኑን በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ ተናገሩ። ፓርቲው ይህን የሚያደርገው ዴሞክራሲ እንዲዳብርና በሀገር ጉዳይ ተቀራርቦ የመስራት ባህል እንዲጎለብት በማሰብ መሆኑን አቶ መለሰ ገልጸዋል። የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ…

Read More

የምስራቅ አፍሪካ ዓመታዊ የፋይናንስ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሔድ ጀመረ::

ለሰባተኛ ጊዜ በሚካሄደው የፋይናንስ ጉባኤ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱን ጨምሮ፣ የባንክ ሀላፊዎች፣ የኢንሹራንስ ተቋማት ተወካዮችና የፋይናንስ ዘርፍ ተዋናዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ። ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ መቋቋም የሚችል ምጣኔ ሀብትን መገንባት፣ በምስራቅ አፍሪካ ትስስርን መፍጠር ፣ ኢኮኖሚያዊ እድሎችን ጨምሮ የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረግ በጉባኤው ለውይይት ከተያዙ አጀንዳዎች ውስጥ ናቸው። በተመሳሳይ ኢትዮጵያ የካፒታል ገበያን በማቋቋም…

Read More

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኢንዱስትሪ ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ አስመዝግቧል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)::

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ አቅሞችን ወደ ስራ በማስገባት ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገቡን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖን አስጀምረዋል። በንቅናቄው አማካኝነት ባለፉት 9 ወራት ከ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ መተካት መቻሉንም ገልጸዋል። በሚሊኒየም አዳራሽ የተከፈተው ይህ ኤክስፖ ዛሬን ጨምሮ ለአምስት…

Read More

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአንዳንድ ኤምባሲዎች የደቦ መግለጫዎች ተቀባይነት እንደሌላቸው አስታወቀ

ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ያደረጉ አንዳንድ ኤምባሲዎች በደቦ የሚያወጧቸውን መግለጫዎች ኢትዮጵያ እንደማትቀበል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ነብዩ ተድላ የሀገሪቱን አበይት የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴዎች አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ አበባ የሚገኙ አንዳንድ ኤምባሲዎች የሚያወጧቸው የጋራ መግለጫዎች ከተለመደው የዲፕሎማሲ አሰራር ያፈነገጡ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት የዓለም የፕሬስ ቀንን ምክንያት በማድረግ አንዳንድ ኤምባሲዎች…

Read More

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ምርት ጥራት ምርመራና ሴርተፊኬሽን ማዕከል በቦንጋ ከተማ ዳግም ሥራ መጀመሩን የማዕከሉ አደራጅ አብይ ኮሚቴ አስታወቀ።

ማዕከሉ ዳግም መከፈቱ ከዚህ ቀደም በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በነጋዴዎች ላይ ይደርስ የነበረዉን ጫና የሚቀነስ ነዉ ስል የካፋ ዞን ቡና አቅራቢዎች እና አዘጋጆች ማህበር ገልጿል። የካፋ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አከባቢ ጥበቃና ሕብረት ሥራ ልማት መምሪያ ኃላፊና የቦንጋ ምርት ጥራት ምርመራና ሴርተፊኬሽን ማዕከል አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጋዎ አባመጫ ቡና ለዞኑ ማህበረሰብ ከባህላዊና ታሪካዊ ቁርኝት ባለፈ ማህበራዊና…

Read More

የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ ችቦ አቀባበልና ሽኝት መርሃ-ግብር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ያሉበት ደረጃ ተገመገመ

በግምገማ መድረኩ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ እንደተናገሩት ጉዳዩ የገፅታ ግንባታና የዞኑን የስፖርት ዘርፍ ለማነቃቃት በዚህም አካባቢያችንን ለዓለም አጉልቶ ለማሳየት ትልቅ ፋይዳ ያለው በመሆኑ እንደ ዞን ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እስከ ታችኛው ወረዳና ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች ተሣታፊዎች በአግባቡ መለየታቸውን ተናግሯል። የቦታ ዝግጅት፣የፓናል መወያያ አዳራሽ የማዘጋጀትና የማስዋብ ሥራ፣ እንግዶችን ለመቀበል የሚያስችል የመስተንግዶና የተሽከርካሪዎች ዝግጅት በስፋት የተሰሩ…

Read More

የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ ችቦ ንቅናቄ መድረክ ከግንቦት 02 – 03 /2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚካሄድ ተገለጸ\::

በክልሉ የፖለቲካና አስተዳደር መቀመጫ በሆነችው ቦንጋ ከተማ ላይ የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ ችቦ አቀባበልና አሸኛኘት በዓል እንደሚደረግ ተገለፀ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት የፖለቲካና አስተዳደር መቀመጫ በሆነችው ቦንጋ ከተማ ላይ የ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ ችቦ አቀባበል በዓል በደማቅ ሁኔታ እንደሚደረግ የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ ተናግረዋል። የቢሮው ኃላፊ በሰጡት መግለጫ መርሀግብሩ በኢትዮጵያ…

Read More

የሥራ ላይ ደህንነትንና የሰራተኞችን መብትና ጥቅም የማስከበር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል – ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል::

የኢንዱስትሪ ሰላምን የማረጋገጥ፣ ምርታማነትን የማሳደግ፣ የሥራ ላይ ደህንነትንና የሰራተኞችን ጥቅም የማስከበር ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ገለጹ። የዓለም የሠራተኞች ቀን በኢትዮጵያ ለ49 ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ135 ጊዜ “ለሠላምና ለኑሮ ውድነት መፍትሔ እንሻለን” በሚል መሪ ሐሳብ እየተከበረ ይገኛል። በአዲስ አበባ በተከናወነው መርሃ ግብር የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ ሌሎች…

Read More