Trendings

Getenesh Gebeyehu

ፋና ወጊ ትሩፋት!ወ/ሮ ሞሚና መሀመድ ፋና ወጊ በሆነ ስራዎቻቸው ለ25 ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠርም የሌሎች ኢትዮጵያዊያንን የኢኮኖሚ ችግር በመቅረፍና ተጠቃሚ በማድረግ የድርሻቸውን በመወጣት ላይ ናቸው።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በህዳር 6/2015 ዓ.ም የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በተገኙበት የአንድ ቀን መነሻ ፖቴንሻል ምልከታና የአንድ ቀን ዉይይት በማካሄድ ክልላዊ የሌማት ትሩፋት ይፋዊ ስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በማድረግ ወደ ስራ መገባቱ ይታወቃል።በሌማት ስራዎች ወደ ተግባር ከተገባ በአንድ ዓመት ውስጥ በርካታ ለውጦች በክልሉ እየተገኙ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ መረጃ ያመላክታል።የሌማት ትሩፋት…

Read More

ይህ የምክር ምዕራፍ በቀጣዩ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ምክክር የሚደረገባቸውን መሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ለመለየቱ ስራ ቁልፍ ሚና አለው – መስፍን አርዓያ(ፕ/ር)

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የከተማ አስተዳደርና ክልላዊ የምክክር ምዕራፍ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ተጀምሯል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ÷ ኮሚሽኑ በምሁራን ፣ልሂቃንና በተለያዩ የፖለቲካ ተቋማት ጥያቄ የመንግስት ፈቃድና ፍላጎት ታክሎበት በ11 ክልሎችና ሁለት ከተማ አስተዳደሮች በሚገባ ተቃኝቶ መቋቋሙን አውስተዋል፡፡ የተደራጁ የሃይማኖት፣ የሲቪል ማህበረሰብ እና የፖለቲካ ተቋምትን በየደረጃው በማካተት በ4 ምዕራፍ በከፋፈላቸው…

Read More

የኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ አመራሮች ካውንስል ተመሠረተ

በዚሁ ወቅት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እንደተናገሩት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለሀገራዊ ልማት በመካከለኛና ዝቅተኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሃይል በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። ተቋማቱ የክህሎትና የዕውቀት ሽግግር በማድረግ ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ተመሳሳይ ተልዕኮ ካላቸው ተቀማት ጋር ያላቸውን ግንኙነት በተደራጀ መልኩ ለማሳለጥ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ዘርፉን…

Read More

የህዝቦችን ተጠቃሚነትና የተመጣጠነ እድገት ለማረጋገጥ ገቢ የማመንጨት አቅምን ማጠናከር ይገባል፡- አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

የህዝቦችን ተጠቃሚነትና የተመጣጠነ እድገት ለማረጋገጥ ገቢ የማመንጨት አቅምን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት ያዘጋጀው የጋራ ገቢዎች አስተዳደርና ክፍፍልን በተመለከተ የፌዴራልና የክልል ባለድርሻ አካላት የጋራ ምክክር መድረክ በሀዋሳ እየተካሄደ ነው። በመድረኩ የተገኙት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር እንደገለጹት፤ የሀገሪቱ የጋራ ገቢዎች ቀመር ከ20…

Read More

የጋራ ዕሴቶችን በማጎልበት ክልላዊ አንድነትን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ።

በቴፒ ከተማ ስካሄድ የነበረው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ብሔረሰቦች ምክርቤት 2ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም በመገምገምና በቀጣይ የትኩረት መስኮች ላይ በመምከር ተጠናቋል። በጉባኤው የዘጠኝ ወራት ዝርዝር የተግባር አፈጻጸም በምክር ቤቱ ምክትል አፌ ጉባኤ የተከበሩ አቶ መለሰ ከበደ ቀርቧል። በዚህም ምክር ቤቱ በህገመንግስቱ በተሰጠው ስልጣን መሠረት በጋራ…

Read More

በክልሉ የተገኘውን ሠላም ለማጽናት የምክር ቤቱ አባላት የሠላም አምባሳደርነትን ሚና መጫወት እንዳለባቸው ተመላከተ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የበሔረሰቦች ምክርቤት በአሰራርና አባላት ሥነምግባር ድንብ እና ዘላቂ ሠላም ግንባታ ዙሪያ ለምክር ቤት አባላት በቴፒ ከተማ ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ የተሳተፉ የባለድርሻ አካላት በክልሉ የተገኘውን አንጻራዊ ሠላም ለማጽናት የምክር ቤቱ አባላት የሠላም አምባሳደርነትን ሚና መጫወት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በክልሉ ከጥቂት አመታት በፊት ይስተዋል የነበረውን የሠላም መደፍረስ በንግግርና ወይይት በመፍታት ችግር ዉስጥ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በበልግ ግብርና ስራዎች የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እየተሻሻለ መምጣቱ ተገለጸ ፡

በ2016 የበልግ አዝመራ ወቅት በክልሉ ከ354 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል ፡፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በመገባቱ የተሻለ አፈጻጸም እየታየ ነው ፡፡ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የአፈር ማዳበሪያና የምርጥ ዘር አቅርቦት መሻሻሎች እንዳሉት ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች ተናግረዋል ፡፡ በቤንች ሸኮ ዞን በሰብል አብቃይነቱ ከሚታወቁት…

Read More

በአዲስ አበባ አጀንዳ የማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ ዛሬ ይጀመራል

በአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ መርሃ ግብር የሚሳተፉ የህብረተሰብ ተወካዮች ወደ ተዘጋጀው ቦታ እየተሰባሰቡ ይገኛሉ። በአዲስ አበባ ከተማ በሚካሄደው የምክክር ምዕራፍ ከ2 ሺህ 500 በላይ ተወካዮች እንደሚሳተፉ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል፡፡ በምክክር ምዕራፍ መርሃ ግብሩ ሶስት ዋና ዋና ተግባራት የሚከናወኑ ሲሆን እነሱም ተሳታፊዎች በምክክርና በውይይት የአጀንዳ ሀሳቦችን ማምጣት፣ አጀንዳዎቻቸውን የጋራ በማድረግ ያሰባስባሉ፣ ያደራጃሉ እንዲሁም…

Read More

“ቢስት ባር” የቤንች ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል የዓለም ዓቀፍ የባህል ሀብት ሊሆን በሚችል መልኩ ባህላዊ ዕሴቱንና ይዘቱን በጠበቀ አኳኋን ለማክበር እየተሰራ መሆኑን የቤንች ሸኮ ዞን ባህል፣ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ አስታወቀ::

የብሔረሰቦች በዓላት እንደ ብሔረሰቡ ማንነት፤ አሰፋፈር፣ ባህላዊ የዘመን አቆጣጠርና ወቅቶችን መሰረት በማድረግ በጋራ በመሰብሰብ ያከብራሉ፡፡በዚህም ወቅቱን የሚዋጅና እርስ በእርስ የሚያስተሳስራቸውን የጋራ አጀንዳ ይቀርፃሉ፤ ይነጋገሩበታል፤ ይወቃቀሱበታል ያለፈውን የአሁንና የወደፊቱ ታሪካቸው ዙሪያ ይወያያሉ፤ ይከራከራሉ፤ ያርማሉ፤ ያደራጃሉ፤ ያለማሉ ለቀጣዩም ትውልድ ያሸጋግራሉ፡፡በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት 13 ነባር ብሔር፣ ብሔረሰቦች ከሌሎች የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ጋር ተዋደው፣ ተዛምደውና…

Read More

የምስራቅ አፍሪካ አገራት የባለብዙ ወገን ትብብራቸውን በማጠናከር ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት በጋራ ሊሰሩ ይገባል

የምስራቅ አፍሪካ አገራት የባለብዙ ወገን ትብብራቸውን በማጠናከር ለቀጣናው ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ተመራማሪዎች ገለጹ። በምስራቅ አፍሪካ የሚስተዋለው የኃይል ፉክክር በአካባቢው ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር ፈተና እየሆነ መምጣቱንም አመላክተዋል። ምስራቅ አፍሪካ የአውሮፓ መካከለኛው ምስራቅና አፍሪካ የሚተሳሰሩበት ስትራቴጂካዊ ቀጣና ሲሆን፤ የዓለም ፖለቲካዊ ምጣኔ ኃብታዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴ መዘውር እንደሆነ ይታወቃል። ኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምስራቅ ጋር…

Read More