በረመዳን ጾም ወቅት የታየው የመረዳዳትና የመደጋገፍ መልካም እሴት በሌሎች ቀናትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል የእምነቱ ተከታዮች ጠይቀዋል፡፡
ከአምስቱ የእስልምና መሠረቶች አንዱ የሆነዉ የኢድ አልፈጥር በዓል በመላው አለም በሚገኙ የእምነቱ ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበር ታላቅ በዓል ነው፡፡ በዓሉም ከአንድ ወር የረመዳን ጾም ማብቂያን ተከትሎ በድምቀት የሚከበር ሲሆን ዘንድሮም በሂጅራ አቆጣጠር ለ1 ሺህ 4 መቶ 45ኛ ጊዜ በተለያዩ አካባቢዎች በድምቀት ተከብሯል፡፡ ከእነዚህም በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ተገኝተን ያነጋገርናቸዉ የእምነቱ ተከታዮች በሰጡት አስተያየት ያለፈው የጾም…
