ስታርት አፕ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንድትሆን የሚያስችሉ ናቸው፦የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር::
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንድትሆን ስታርትአፖች መበራከት እንደሚገባቸው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ። በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰላምይሁን አደፍርስ ከኢቢሲ ሳይበር ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ስታርትአፕን ለማበረታታት እየተሞከረ መሆኑ በመጥቀስ ቀጣይነት እንዲኖራቸው እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡ የስታርትአፕ ሀሳብ ያላቸው ሁሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ እና ተዘጋጅተው የሚመጡባቸው ምቹ መድረኮች እንዲኖሩ እየተሰራ ይገኛል የሚሉት ኃላፊው…
